Hadiyyooma Media Network - HMN

Hadiyyooma Media Network - HMN Hadiyyooma Media Network
(2)

በሕዝብ ተሳትፎ የተገነባው የጊምቢቹ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት ተመረቀ።ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ ከጊምቢቹ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተወሰደ 900 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፤ ግንባታው ከ2...
03/09/2026

በሕዝብ ተሳትፎ የተገነባው የጊምቢቹ ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት ተመረቀ።
ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍቱ ከጊምቢቹ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተወሰደ 900 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፤ ግንባታው ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት አራት ዓመታት ከሕዝብ በተሰበሰበ ሀብት ሲከናወን መቆየቱ ተገልጿል።

ከተማዋ ለተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ማዕከል በመሆኗም ቤተ-መጽሐፍቱ በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ እንደሆነ ታምኖበታል።

በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ ድላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፣
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣ ምክትል ርዕሰ-መስተዳደርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
https://www.facebook.com/hadiyyooma

ምክር ቤቱ ለ2019 በጀት ዓመት 15ቢሊየን 490 ሚሊዮን 720 ሺህ 181 ብር በጀት አጸደቀ የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሔደ ነው ...
02/09/2026

ምክር ቤቱ ለ2019 በጀት ዓመት 15ቢሊየን 490 ሚሊዮን 720 ሺህ 181 ብር በጀት አጸደቀ

የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሔደ ነው ።

ምክር ቤቱ በሁለተኛ ቀን ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበለትን ረቂቅ በጀት መርምሮ 15ቢሊየን 490 ሚሊዮን 720 ሺህ 181 ብር በጀት አጽድቋል።

ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር 15.14%ብልጫ እንዳለ ተመላክተዋል።

🔹ከክልል መንግሥት ግምጃቤት 6 ቢሊዮን 648ሚሊዮን 869ሺህ 314ብር፣
🔹ከዞኑ መደበኛ ገቢ 6ቢሊዮን 513ሚሊዮን 380ሺህ 37ብር፣
🔷ከጤና ተቋማት ገቢ 231ሚሊዮን 343ሺህ 799 ብር፣
🔷ከትምህርት ቤት ገቢ 223 ሚሊዮን 816ሺህ 189 ብር፣
🔷ከመዘጋጃ ቤት ገቢ 1ቢሊዮን 831ሚሊዮን 725ሺህ 938 ብር
🔷ከውጭ እርዳታ 41ሚሊዮን 584ሺህ 904 ብር ሆኖ ተዘርዝሯል።

የሀዲያ ዞን ፋይናንስና ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ዱናሞ የዞኑን በ2019 በጀት አመት ሥራ ላይ የሚውል ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በዚህም በቀጣይ በጀት ዓመት በዞኑ ገቢ አሰባሰብ ላይ ልዩ ትኩረት መስጣት እንዳለበት የሚያመላክት ነገር መኖሩን ጠቁመዋል።

አስቾካይ የእርዳታ ጥሪ፦በሀዲያ ዞን የሻሾጎ ወረዳ  ሸሞ ቦዮ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው  ወጣት እስያስ ኃይሌ(ደብቤ) በሕገወጥ  ደላሎች  ታታሎ ቤተሰቡን ሳያመክርና ሰያሰወቅ  ወደ አውሮፓ አገራት...
02/09/2026

አስቾካይ የእርዳታ ጥሪ፦
በሀዲያ ዞን የሻሾጎ ወረዳ ሸሞ ቦዮ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት እስያስ ኃይሌ(ደብቤ) በሕገወጥ ደላሎች ታታሎ ቤተሰቡን ሳያመክርና ሰያሰወቅ ወደ አውሮፓ አገራት በመሄድ ላይ እያለ በሊብያ አገር በወንበዴዎች እጅ በመወደቅ 1600000(አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሽ ብር) እንድካፈል አለበለዚያ ሕይወትን እንደሚያጠፋ የተነገረው ስሆን ቤተሰቡ አቅመ ደካማ በመሆኑ የተቻላችሁን እርዳታ በመስጣት የወጣት እስያስ ኃይሌ ሕይወት እንታደግ እያለን
የወላጅ አበቱ አካውንት ማለትም አቶ ኃይሌ ታደሰ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000210424982/1000165269962
ለበለጠ መረጃ 0921893532 በመደወል ሙሉ መረጃ መገኘት ይችላሉ ።

''ሰውን  ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው።''በሚል መሪ ቃል   የተመሠረተው ማቴዮም መላዬ የተሰኘው  በጎ አድራጎት  ማህበር  በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ደቡብ በሌሣ ቀበሌ  ከ2011ዓ/ም ...
01/09/2026

''ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው።''በሚል መሪ ቃል የተመሠረተው ማቴዮም መላዬ የተሰኘው በጎ አድራጎት ማህበር በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ደቡብ በሌሣ ቀበሌ ከ2011ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ ችግር ምክንያት ትምህርት መማር ላልቻሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ በማሟላት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ በማድረግ ላይ የሚገኝ ማህበር ነው።
ይህ የበጎ አድራጎት ማህበር በ2019 የትምህርት ዘመን የተለመደውን የትምህርት ቁሳቁስ
ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች ለመቅረብ የተለያዩ ባለሀብቶች ፣ የሃይማኖት ተቋማት ፣ በተላያዩ ሀገራት የምኖሩ የአካባቢው ዲያስፖራ አባለት እንድሁም በችግር ላሉ ተማሪዎችን ለማገዝ ፍላጎት ያላችሁን ሁሉ የተለመደውን ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪውን ያቀርባል ።

የማህበሩ አካውንት በማህበሩ አስተባባሪዎች ማለትም በአቶ ግርማ ሽጉጤ ፣በአቶ ቢላሊ ሀሊል እና በአቶ ተሾመ መሐመድ የተከፈተው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000293990957 ስለሆነ የበኩላቸውን ድጋፍ እንድታደርጉ እንላለን ።
የማቴዮም መላዬ አስተባባሪዎች

Hadiyyooma Media Network - HMN

01/09/2026

አብቹ ለኢትዮጵያ መንግስት የሕዝብ ምስክርነት - HMN

01/09/2026

ሆሳዕና ቅ/ ሥላሴ ካቶሊክ ትምህርት ቤት በልዩ መጠሪያ አባ ትምህርት ቤት በሚል የሚታወቀው ገደም ስታዊያን ከ200 በላይ ተማሪወች ላይ ልዩ እርምጃ ተወሰደ !

የሀድያ ዞን ምክር ቤት 27ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 26 እስከ 27/2018 ዓ.ም ያካሂዳል::የሀድያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 26 እስከ...
31/08/2026

የሀድያ ዞን ምክር ቤት 27ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 26 እስከ 27/2018 ዓ.ም ያካሂዳል::
የሀድያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 26 እስከ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያካሂድ የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ አስታወቁ።

ዋና አፈ ጉባኤዋ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ ምክር ቤቱ በሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታው በሚቀርቡለት ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል።

ምክር ቤቱ በጉባኤው በሚከተሉት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ይመክራል፦

👉የ4ኛ ዙር 13ኛ የሥራ ዘመን 26ኛ መደበኛ ጉባኤ እና የ7ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ቃለ ጉባኤዎችን መርምሮ ማፅደቅ፤

👉የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እንዲሁም በልማትና መልካም አስተዳደር ረገድ በተከናወኑ ተግባራት ላይ በጥልቀት መወያየት፤

👉የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅዶችና አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቶ ማፅደቅ፤

👉የሀድያ ዞን ምክር ቤትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት መርምሮ ማፅደቅ፤

👉የዞኑን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ መርምሮ ማፅደቅ፤

👉የዞኑን የ2019 አጠቃላይ በጀት መርምሮ ማፅደቅ።

ለዚሁ መደበኛ ጉባኤ ዝግጅቶች በሙሉ መጠናቀቃቸውን ዋና አፈ ጉባኤዋ ክብርት ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ አረጋግጠዋል።

30/08/2026

ለእዉነት እንኑር !!

30/08/2026
30/08/2026

#የሀዲያ ከቤረ ሙዚቃ 🎧 - HMN

Address

Johannesburg Central
2001

Telephone

+27718240957

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiyyooma Media Network - HMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Hadiyyooma Media Network - HMN:

Share

Category