Woldia Times

Woldia Times ሕዝባዊና አካባቢያዊ ችግሮችን እንዳስሳለን፣ መረጃ እናቀርባለን እንዲሁም የመፍትሄ አቅጣጫ እናሳያለን! ግባችን ሕዝባዊ ተጠቃሚነት ነው።
(1)

ወልድያ ከተማ  31 ኪሎ ሜትር ስኩዌር የቆዳ ስፋት ላይ ያረፈ የዞን ከተማ ነው። አስመራ 45 ኪሎ ሜትር ስኩዌር ይዞታ ላይ ያረፈች የአንዲት ሀገር ዋና ከተማ ነች! ለጠቅላላ እውቀትዎ እንጨ...
16/06/2026

ወልድያ ከተማ 31 ኪሎ ሜትር ስኩዌር የቆዳ ስፋት ላይ ያረፈ የዞን ከተማ ነው።

አስመራ 45 ኪሎ ሜትር ስኩዌር ይዞታ ላይ ያረፈች የአንዲት ሀገር ዋና ከተማ ነች!

ለጠቅላላ እውቀትዎ እንጨነቃለን!

16/06/2026
15/06/2026

ክንድ አለሜ ና ና

ጥያቄ! ፎቶ አንሺው የት ቦታ ላይ ቆሞ ነው ይሄን የሚገርም ፎቶ ያነሳው?
15/06/2026

ጥያቄ! ፎቶ አንሺው የት ቦታ ላይ ቆሞ ነው ይሄን የሚገርም ፎቶ ያነሳው?

ልጅና ሐውልት ይውጣልሽ ተብላ የተመረቀችው ወልድያ!( #ተስዓለ)​የምድር ላይ ትልቁ ድንቅ ነገር ታሪክን መሥራት ብቻ አይደለም፤ የተሠራውን ታሪክ በትውልድ ልብና በዓለት ላይ ቀርጾ ማስቀረትም...
14/06/2026

ልጅና ሐውልት ይውጣልሽ ተብላ የተመረቀችው ወልድያ!
( #ተስዓለ)

​የምድር ላይ ትልቁ ድንቅ ነገር ታሪክን መሥራት ብቻ አይደለም፤ የተሠራውን ታሪክ በትውልድ ልብና በዓለት ላይ ቀርጾ ማስቀረትም ጭምር እንጂ። የታሪክ ማህደር፣ የሊቃውንትና የጀግኖች ማፍሪያ የሆነችው ወልድያ ከተማ፣ በቅርቡ ያደረገችው ታላቅ ኩነት የዚሁ እውነት ማሳያ ነው።

ከተማዋ "ልጅና ሐውልት ይውጣልሽ" ተብላ የተመረቀች ይመስል፣ የውጤታማነት፣ የጽናትና የዕውቀት ተምሳሌት ለሆኑት ለክቡር ዶክተር አረጋ ይርዳው በሕይወት እያሉ የሰላምና የዕውቀት ማማ የሆነ ድንቅ ሐውልት አቁማላቸዋለች። ይህ ውሳኔና የተሰራው ሐውልት ውበት፣ ከቀላል መታሰቢያነት በላይ የሰነቀ፣ ማረጋገጫም መደነቂያም የሆነ ታላቅ ኩራት ነው።

​በኢትዮጵያ ባህል አብዛኛውን ጊዜ ሰዎችን በሞት ካጣናቸው በኋላ ማሞገስና መዘከር የተለመደ በሆነበት ሥርዓት ውስጥ፣ ወልድያ ይሄንን የተለመደ መንገድ ሰብራ መውጣቷ በእጅጉ ያስደንቃል። ዶክተር አረጋ ይርዳው በሕይወት ዘመናቸው፣ በቁማቸው፣ በለገሱት ዕውቀትና ባበረከቱት የላቀ አበርክቶ ልክ እንዲህ ያለ መሳጭና ገላጭ ሐውልት ሲቆምላቸው ማየት ለሀገር ትልቅ ትምህርት ነው።
"ለአንጋፋው ምሁር በሕይወት እያሉ እውቅና መስጠት፣ ለነገው ትውልድ ስኬትን በቁም የመሸለም ባህልን መትከል ነው" የሚለውን የዶክተሩን የሕይወት ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ክስተት ነው።

​የሐውልቱ አሠራርና ይዘት ራሱ በእጅጉ ገላጭና ምስጢር የሰነቀ ነው። ከተራ ድንጋይነት አልፎ የባለታሪኩን የሕይወት ፍልስፍና ይናገራል። ዶክተር አረጋ ይርዳው የመማር፣ የማያቋርጥ ጥረት እና የላቀ ስኬት አብነት (Role Model) ናቸው። ያሳለፉት የኮርፖሬት አመራር ሕይወት፣ ያበረከቷቸው የአመራር ጥበብ ስራዎችና ለከፍተኛ ትምህርት የሰጡት ትኩረት ሁሉ በዚያ ሐውልት ግርማ ሞገስ ውስጥ ይንጸባረቃል። ሐውልቱ ዝም ብሎ የቆመ ዓለት ሳይሆን፤
​ዕውቀት ከልፋትና ከጽናት ጋር ሲጋባ የምድርን ስበት አሸንፎ እንዴት ማማ ላይ እንደሚወጣ፣ ​አመራር (Leadership) ማለት ሰዎችንና ተቋማትን ወደ ላቀ ከፍታ የመውሰድ ጥበብ መሆኑን፣ ​ውጤታማነት ደግሞ በትውልድ ልብ ውስጥ የማይደበዝዝ አሻራ ጥሎ ማለፍ መሆኑን በዝምታ የሚሰብክ ሕያው መጽሐፍ ነው።

​ይህንን ድንቅ ስራ ስንመለከት፣ ወልድያ ልጅን አምጣ፣ በልጅዋ ኮርታ፣ የልጅዋን ክብር ሐውልት ቀርጻ ሴታቆምና ፍቅሯን ለትውልድ ስታቆም ደግሞ "እውነትም ልጅና ሐውልት ይውጣልሽ!" የተባለች ከተማ ያሰኛታል። ይህ ሐውልት ለዶክተር አረጋ ይርዳው የተሰጠ ክብር ብቻ አይደለም፤ የወልድያ ወጣቶችና መላው የኢትዮጵያ ትውልድ ሐውልቱን በተመለከቱ ቁጥር "እኔስ ለሀገሬ ምን እሠራለሁ? በጽናት ከተማርኩና ከሠራሁ እንደዚህ እከበራለሁ" ብለው ስኬትን እንዲያልሙ የሚያደርግ የብርታት ምንጭ ነው።

​ወሎየው ምሁር፣ የሥራና የዕውቀት አርበኛው ዶክተር አረጋ ይርዳው ለሀገር ያበረከቱት ውለታ በዓለት ላይ ታትሞ ለዘላለም ይኖራል። ወልድያ ሆይ፣ ታላቅ ልጅሽን በቁሙ ስላከበርሽ፣ በዕውቀት ማማ ላይ ለደረሰ መሪ የሚመጥን ገላጭ ሐውልት ስላቆምሽ ክብር ይገባሻል!!!!
ደጋግሞ ልጅ ይውጣልሽ። ሰላምሽን ያብዛው።
አበቃሁ። #ተስዓለ ካለሁበት።

Tesfaye Alemnew Asmare

እማኝነት ስለ ዶ/ር አረጋ ይርዳው ከብዙ በጥቂቱ!ከዶ/ር አረጋ ይርዳው ጋር ለበርካታ አመታት አብሬ የመሥራት ዕድልን አግኝቻለሁ!ሚድሮክ ቴክኒዮሎጅ ግሩፕን ከጅማሬው አካባቢ አንስቶ ቺፍ ኤግዚ...
14/06/2026

እማኝነት ስለ ዶ/ር አረጋ ይርዳው ከብዙ በጥቂቱ!

ከዶ/ር አረጋ ይርዳው ጋር ለበርካታ አመታት አብሬ የመሥራት ዕድልን አግኝቻለሁ!

ሚድሮክ ቴክኒዮሎጅ ግሩፕን ከጅማሬው አካባቢ አንስቶ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ሆነው ሲያደራጁና ሲመሩ በሩቅም በቅርብም አውቃቸዋለሁ!

እርሳቸው ይመሯቸው የነበሩትን ኩባንያዎች ማስታወቂያዎችም ለ10 አመታት በብቸኝነት ሠርቻለሁ!

ከኤልፎራ እስከ ኤም ቢ አይ - ከሆም ዴፖ እስከ ዋንዛ - ከድል ቀለም እስከ ኮስፒ - ከለገደምቢ ወርቅ ማዕድን እስከ ደሴው ሃጅ መሀመድ ያሲን ህንፃ ዶኪዩመንተሪ ፊልሞችን ሠርቻለሁ!

1997 ታህሳስ ላይ "ዕጣ ፈንታ" የተሰኘውን ፊልሜን በአአ ቲአትርና ባህል አዳራሽ ተገኝተው በክብር እንግድነት የመረቁልኝም እሳቸው ናቸው!

ወልዲያ ስታዲየም ሊገነባ መቻሬ ላይ የመሠረት ድንጋይ ሲጣልም፣ ለግንባታው ገቢ ማሰባሰቢያ ሲደረግም፣ ስታዲየሙ በሼህ መሀመድ አንጡራ ተገንብቶ በድምቀት ሲመረቅም አብሬአቸው ነበርኩ!

ወልድያ ያደጉበት ቤት ገብቼ ያኔ በህይወት የነበሩትን ወላጅ አባታቸውን በአክብሮት ዘይሬአለሁ!

የጋራ ትምህርት ቤታችን ወ/ሮ ሲኅን 75ኛ አመት ስናከበር ለድምቀቱም ለስኬቱም የዶ/ር አረጋ ይርዳው ድርሻ የትየለሌ ነበር!

ዶ/ር አረጋ ከኩባንያዎቻቸው ባሻገር ለወሎና ለወሎ ህዝብ ያላቸውን መንገብገብ፣ መልካም ምኞትና ተግባራዊ ሥራ በቅርበት ተመልክቻለሁ!
ይህ ከብዙው እጅግ በጣም ጥቂቱ የእውቂያ መንገዴ ነው!

እነሆ ከሰሞኑ እኒህ በአጠቃላይ ለሀገር ብዙ ይጠቅማል ያሉትን የሠሩ፣ ሃሳባቸውን ሳይሰስቱ ያጋሩ፣ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ምሁር፣ አሳቢና የሥራ መሪ፤ ባደጉበት፣ በተማሩበትና ክፉ ደጉን ባዩበት ወልድይ ከተማ ላይ፤ ስለሠሯቸው መልካም ሥራዎች ሁሉ ምስክር ይሆንላቸው ዘንድ፤ በስታዲየሙ ምረቃ ወቅት በስማቸው በተሰየመላቸው ጎዳና ላይ ሐውልት እንደቆመላቸው ስሰማ በእጅጉ ደስ አለኝ!

የሚገባ ነገር ለሚገባው ሰው ሲኾን እንዲህ ያስደስታል!
ወልድያዎች ገለታ ይግባችሁ!
ደግ ማፍራቱን ታውቁበታላችሁና አሁንም ብዙ ደግ፣ ብዙ መልካም ታፈሩ ዘንድ እመኛለሁ!

Mamo

ወልድያ ከተማ ከ40 ከተሞች የተወጣጡ አመራሮችን በመቀበል የልማት ተሞክሮዋን እያጋራች ትገኛለች። በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ ውጤታማ የልማት ስራዎችን ለመመልከት ለተገኙት ከተሞች ከንቲባዎ...
12/06/2026

ወልድያ ከተማ ከ40 ከተሞች የተወጣጡ አመራሮችን በመቀበል የልማት ተሞክሮዋን እያጋራች ትገኛለች። በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ ውጤታማ የልማት ስራዎችን ለመመልከት ለተገኙት ከተሞች ከንቲባዎች እና የመሰረተ ልማት ስራ አስኪያጆች ተሞክሮው ቀርቦላቸዋል ።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በቅርቡ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑትን የሳይንስ ካፌና የፈጠራ ማዕከል፣ የሞሰብ አንድ ማዕከልን እንዲሁም የባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ (አያ ሙሌ) የሕዝብ ዲጂታል ቤተ መጻሕፍትን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማና መሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፣ በአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ደሳለኝ፣ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) እና የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ተገኝተዋል።

Address

Woldia

Telephone

+17735642986

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Woldia Times:

Share