19/05/2026
«ሂዶቴ» አዲስ ፊልም ለተመልካቾች ሊቀርብ ነው
| በሴት ልጅ ጥቃትና አስከፊው የሴት ልጅ ግርዛት ዙሪያ የሚያጠነጥነው «ሂዶቴ» የተሰኘው አዲስ ፊልም በቅርቡ ለተመልካቾች ይቀርባል ተብሏል።
ፊልሙ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባው የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እና በጀርመን ፍራይቡርግ ከተማ በልዩ ስነ-ስርዓት ለእይታ ይበቃል።
«ሂዶቴ» የወላይትኛ ቃል ሲሆን «ተስፋ» ማለት ነው።
የፊልሙ ዋና ዓላማ ማህበረሰቡ ከሴቶች ጎን እንዲቆም ማነቃቃትና ግርዛትን መዋጋት ነው።
ፊልሙን ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ ለመስራት ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ሆኖበታል።
በሳሙኤል ተሻገር ተፅፎና ዳይሬክት ተደርጎ በታምራት በርሄ ፕሮዲውሰርነት የተዘጋጀ ነው።
ፊልሙ 1 ሰዓት ከ30 ደቂቃ የሚረዝም ሲሆን ለመስራትም 1 ዓመት ፈጅቷል።
75% በወላይታ ዞን እና 25% በሀዋሳ ከተማ የተከናወነ ሲሆን 1 ወር ፈጅቷል።ፅናት ተረፈ፣ ሄኖክ አለማየሁ፣ አማኑኤል የሺወንድና ናርዶስ አንትዋ በዋናነት ተሳትፈዋል።
170 አጃቢ ተዋንያንና 24 ባለሙያዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 215 ሰዎች ተሳትፈውበታል።
ፊልሙ በእንግሊዝኛና ጀርመንኛ ንዑስ ርዕስ (Subtitles) የተዘጋጀ ነው።
ከአገር ውስጥ ምርቃት በኋላ ወደ ታላላቅ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ያመራል።
በተጨማሪም በአገር ውስጥ ሲኒማ ቤቶችና በተመረጡ የአፍሪካ አገራት ይታያል።
በአውሮፓ ለሚኖረው ስርጭትም «ግሩምበርግ ፊልም» ከተሰኘ የጀርመን ኩባንያ ጋር የ3 ዓመት የሽያጭ ስምምነት ተፈርሟል።
📷 kebede mekibeb