03/08/2026
" " በሚል ስያሜ ይጠራ በነበረ ሀሰተኛ ሚዲያ አማካኝነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥትና በተለያዩ አመራሮች ላይ የሚያነጣጥሩ መልዕክቶችን በማሰራጨት፣ በሕዝብና በመንግሥት መካከል እምነትን ለማዳከም፣ ጥርጣሬና ክፍፍል ለመፍጠር እንዲሁም የጥላቻ ንግግሮችን በማስፋፋት ተሳትፎ ነበረው ተብሎ የሚነገረው አቶ በላይነህ ባህሩ ፣ በወቅቱ በክልሉ መንግሥት በተደረገ ክትትልና ግምገማ ከኃላፊነቱ መነሳቱ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ፣ ይህ ግለሰብ #በፋኖ ተፈሪ አባቴ አማካኝነት የክልሉን ፓርቲና መንግሥት አሰራር ባልተከተለ መንገድ በሕጋዊና በግልጽ አሰራር ሳይሆን በውስን ግለሰቦች ድጋፍ የሳውላ ከተማ ከንቲባ ሆኖ መሾሙ በአካባቢው ሕዝብ ዘንድ ቅሬታና ቁጣ መፍጠሩ ይነገራል ።
በተጨማሪም፣ ግለሰቡ በያዘው የሥልጣን ኃላፊነት ያልተረካ በመሆኑ፣ የዞን አስተዳዳሪ ለመሆን እስከ ፌዴራል ደረጃ ድረስ ግንኙነቶችን በመፍጠር እየሠራ እንደሚገኝ ይነገራል። ስለዚህ ይህንን ከሥርዓተ ባፈነገጠ መንገድ ወደ ሥልጣን ማማ የወጣውን ግለሰብ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያላገኘ መሆኑን በመገንዘብ የክልሉ መንግሥት ማስተካከያ እርምት እርምጃ እንዲወስድ ከወዲሁ እናሳውቃለን ።
Tilahun Kebede
Adem Farah Ibrahim
Tesfaye Beljige Dara