Mareko media

Mareko media ነፃነቴን ማወጅ

22/05/2026

good content creation

20/05/2026
17/05/2026
15/05/2026

🙏🙏🙏🙏🙏

26/04/2026

02/04/2026

20 ሚሊዮን መደለያ አልቀበልም ያለው ጌታው ገዛኸኝ ተሬሳ በእግረኛው ሚዲያ...

(ዘሪሁን ተዝናኑ በፌስቡክ ገፁ ካጋራዉ የተወሰደ)

ታሪካዊ ቃለ - ምልልስ‼️

"★ እስከ 6ኛ ክፍል አውንታ በርሲሳ በሚለው ስሜ
ነበር የምጠራው ከ6ኛ ክፍል በኋላ
ገዛኸኝ ተሬሳ በሚል ተቀይሯል።

★ አሩሲ አካባቢ ነው የተወለድኩት። በእናቴ በኩል
ሶዶ ጉራጌ ነኝ። አውንታ ማለት የኮባ ተክል ስሩ
አሚቾ የሚባለው ነው።

★ ለረጅም ጊዜ የሰራሁት በፐርፎርመንስ ኦዲተር ነው።

★ ለ15 ዓመት ያህል በፐርፎርመንስ ኦዲተርነት ለ13
መስሪያ ቤቶች አገልግያለሁ። አሁንም እየሰራሁት
ያለሁት ኦዲቲንግ ነው።

★ በ2002 ዓ.ም ነው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አካውንቲንግና
ፋንናንስ አጥንቼ በባችለር ዲግሪ የተመረቅሁት።

★ ከዚህ በፊት የሰራሁባቸው መስሪያ ቤቶች ሌብነትን
ያለማመዱ መስሪያ ቤቶች ናቸው።

★ መንገዶች ኮንስትራክሽን ፣ ኢኮስኮ ፣ የኢትዮጵያ
ንግድ ስራዎች ድርጅት ሌብነትን ከውጭ ሀገር
አስመጥተው ያከፋፈሉ ናቸው።

★ በሰራሁባቸው መስሪያ ቤቶች ብዙ አሳፋሪና ከሰው
አዕምሮ ውጪ ያሉ ድርጊቶች ሲከናወኑ አይቻለሁ።
ይኼንን በመሸሽ ነበር ያሳለፍኩት። ስሸሻቸው
እየተከተሉኝ መጡ። ከሀገር አባረሩኝ።
ፊት ለፊት ስጋፈጣቸው መሮጥ ጀመሩ።
እያሸነፍኳቸውም ነው።

★ ከጀርባዬ ያለው ሀቅ ብቻ ነው።

★ #የፊንቴክን ወንጀል ለፌዴራል ፖሊስ እኔ ነኝ
የጠቆምኩት።

★ ከፌዴራል ፖሊስ ፣ ከቂርቆስ ክ/ከተማ ጋር
በመጠቆምና መረጃ በመስጠት ነው የሰራነው።

★ ኮሚሽነር ብርሃኑ ይኼንን ነገር ከዳር የምታደርስልኝ
ከሆነ የማደርግልህን አታውቅም ብሎ አበረታታኝ።

★ ፊንቴክ ውስጡ የመኪና ሽያጭ ብቻ ሳይሆን የድንበር
ተሻጋሪ ወንጀሎች አሉበት። ህገ - ወጥ የሰዎች
ዝውውር ነበረበት። መኒ ላውንደሪ ነበረበት።
አደገኛ ወንጀሎች ነበሩበት።

★ ወንጀሎቹን መርምሮ ሳይጨርስ ሰዎቹን መያዝ
ጀመረ። ባለቤቱን ዳንኤል ዮሐንስን ያዘው።
ያን ጊዜ ግርማዬ ከሀገር ወጣ።
የዜግነት ድርሻዬን በዚህ ደረጃ ነው የተወጣሁት።

★ ፊንቴክ ማለት ፋይናንስ ቴክኖሎጂ ማለት ነው።
የቻይና ካምፓኒ ነው። ስራው ገንዘብ ማዘዋወር
ነው እንጂ መኪና ማስመጣት አይደለም።
የመኪና አስመጪነት ፍቃድ የለውም።

★ ጅቡቲ ላይ የታዩት መኪናዎች ሿሿ ናቸው።
የተለያዩ ሰዎች ያስመጧቸው እንጂ ፊንቴክ
ያስመጣቸው አይደሉም።
እንደሚመስለኝ ገንዘቡ ሊታጠብ ነው የፈለጉት።

★ 19 አይነት የወንጀል ጉዳዮች ስላሉበት መንግስት
የሚያየው ወንጀሎቹን ብቻ ነው።

★ ባለቤቱ ዳንኤል ዮሐንስ ከዚህ በፊት ሄሎ ታክሲ
የሚባል ድርጅት አቋቁሞ ወደባህልና ቱሪዝም
ሄዶ ተፈቀደለት። የተለያዩ ባህሪያት በማምጣቱ
ተከለከለ።

★ የነፃ ቀረጥ መብቱን ለሌላ መኪና አስመጪ ድርጅት
ሰጠው። በዚህም 401 ሚሊዮን ብር ተላልፏል።

★ ግርማይ ገ/ሚካኤል የተባለው ደግሞ አስካሉካን
ትሬዲንግ በሚል ደቡብ አፍሪካ ለዓለም ዋንጫ
አጓጉዛለሁ ብሎ ብር ይዞ ጠፍቶ በኢንተርፖል
ተይዞ መጥቶ ፍርድ አግኝቶ የተለቀቀ ነው።

★ ዳንኤል ዮሐንስና ግርማይ ገ/ሚካኤል
3.5 , 3.5 ሚሊዮን ብር አዋጥተው በ7 ሚሊዮን ብር
በጋራ ፊንቴክን መሰረቱ።
ዳሰማን ደግሞ ዳንኤል ዮሐንስና እስቲፋኖስ ዮሐንስ
በጋራ የመሰረቱት ነው። ላይፍ ላይን ኢንቨስትመንት
የሚባል ደግሞ አለ። አመጣጡ መስመሩ ይኼ ነው።

★ ከጀርባ ሆነው ነበር ስራውን የሚሰሩት።

★ በመታሰራቸው አላዝንም።

★ ኢትዮጵያ ውስጥ ሌብነት በህግ አግባብ ፍርድ
ሊሰጠው ይገባል።

★ በአደባባይ የስቅላት ወንጀል ሆኖ ሲበየን ብቻ
ነው ብዬ የማስበው።

★ በአሳሳች ማስታወቂያ ምክንያት ህብረተሰቡን
አሳስታችኋል ብሎ መንግስት ከያዛቸው
እኔ ልሆን አልችልም።

★ በ7 ሚሊዮን ብር ካፒታል መኪና እናስመጣለን ያለን
ካምፓኒ አላዩትም ማለት ነው። ወይም አይተውት
ችላ ብለው አልፈውታል ማለት ነው።

★ አንድ ማስታወቂያ ሲሰራ ህጋዊነቱን ማረጋገጥ
የማስታወቂያ ሰራተኛው ሀላፊነት ነው።
በፍትሀብሔርም ያስቀጣል። በውስጡም
ወንጀል አለበት።

★ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የፓርላማ አባል ስለሆኑ
ያለመከሰስ መብት አላቸው። ያለመከሰስ
መብታቸውን አስነስቶ ወደ ፍርድ ቤት ማቅረብ
የፖሊስና የፍትህ ሚኒስትር ስራ ነው።
ፓርላማውም ሀላፊነት አለበት።

★ ሌሎች ያልተያዙም አሉ። ድምፃዊ ታደለ ሮባም አለ።
የፊንቴክ አምባሳደር ነው። ጋዜጠኛ ትዕግስትም አለች።
ሁለት ቲክቶከሮችም አሉ።እነሱን የመያዝ የመልቀቅ
የኔ ፋንታ አይደለም። የፖሊስ ፋንታ ነው።
ፖሊስ ሊተዋቸው ወይም ሰሞኑን ሊለቀሙ ይችላሉ።

★ አብርሃም ግዛው አንድ ቦታ ላይ ብቻ አልነበረም።
ሄሎ ታክሲ ላይ ፊት ለፊት ታየዋለህ።
ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ላይ በየቦታው ታየዋለህ።
ዳሱማ ትሬዲንግ ላይ እንደገና ታየዋለህ።
ሳያውቁ ነው ልትለኝ አትችልም።

★ የፖሊስ ሪፖርት እንደሚያመለክተው እያንዳንዳቸው
8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መኪና ተሸልመዋል።
ይኼ ከገንዘቡ ውጪ ነው።

★ መንሱር ጀማልን ደጋግሜ ነካካሁት። ደጋግሜ ስነካካው
ሚዛኑን ሳተ እና ተሳደበ። የኔ ድክመት መልኬ ሆኖ
ታየው። ተሳደበ እና ፖሰተ።

★ መንግስት የሚለቀው ከሆነ ተምሮ ሰቃይ ተማሪ
ሆኖ ይወጣል የሚል ተስፋ አለኝ።

★ ወንጀል እና ክፋት ይለያያል።

★ በዚህ ጉዳይ ብራቸውን ከተበሉ ሰዎች ውስጥ
ቂርቆስ ክ/ከተማ ራሱን አንቆ የገደለ ሰው አለ።
ከዚህ ሰውዬ ጀርባ ልጆች አሉ። ቤተሰብ አለ።
አንደኛው ኩላሊቱን ዲያለሲስ የሚያደርግ ነው።

★ ማስታወቂያ የፍትሀብሔር ጉዳይ አይደለም።
እስከ 5 ዓመት ሊያሳስር ይችላል።

★ ለወንጀለኛ እስከተባበርክ ድረስ ወንጀለኛ ነህ።

★ ንግድ ፍቃዱን አልተመለከቱም። የራሳቸውን ገንዘብ
ብቻ ነው የተመለከቱት።

★ ቢመለከቱት ኖሮ እንደ እነ ሉላ ገዙ ፣ ዕፀገነት አበበ
እና አምለሰት ሙጬ ይኼ ማስታወቂያ ይቅርብኝ
ይሉ ነበር። እነ ሉላ ያዩት ነገር ስላለ ነው ይቅርብን
ያሉት።

★ ሰራዊት ፍቅሬ ከዚህ በፊት ሲኖትራክ ይመጣላችኋል
ብሎ ገንዘባቸውን የተበሉ ሰዎች ብዙ ናቸው።

★ ሰለሞን ቦጋለ ለሆስፒታል ብሎ ብዙ ብር ለቅሞ
እስካሁን ገንብቶ አላየነውም። ገንብቶ ብናየው
እናከብረው ነበር። እስካሁን ግልፅ የሆነ ነገር የለም።

★ ዜጋ ዜጋ ነው። ሲኒየር ዜጋ የሚባል ነገር የለም።
ማንኛውም ሰው ወንጀል እስከፈፀመ ድረስ
በሕግ እኩል ነው።

★ የሌብነት ሲስተሙ ጨምሯል። አደገኛነቱ ጨምሯል።

★ ገንዘባቸውን የተበሉ ሰዎች ጀርባቸው ብዙ ቁስል አለ።
ያ ቁስል አንተንም ሊሰማህ ይገባል። ሰራዊት ፍቅሬም
ሊሰማው ይገባል። ሁላችንም ሊሰማን ይገባል።
ገንዘባቸውን ወይም መኪናቸውን ቢያገኙ ከእኔ በላይ
ደስተኛ የለም።

★ በረከት ገበሬዋ ለፌዴራል ፖሊስ ከሳኝ ነበር።
አንድ ሺህ ዳላር ሰጥቼዋለሁ ካለች ማስረጃ ታምጣ።

★ ሰሞኑን ደግሞ ወደ እርዳታ ድርጅቶች እንሄድባቸኋለን።
ቤ/ክርስቲያን ፣ መስጂድ ቸርች ውስጥም አሉ።

★ ከሚገባው በላይ የሚያከብሩኝና የሚወዱኝ ሰዎች
አሉ። የነሱን ቃል ጠብቄ እሄዳለሁ።

★ ስራዬ ከመንግስት ጋርም ሆነ ከፓርቲ ጋር ምንም
አይነት ግንኙነት የለውም።

★ የእኔን ኮንተንት አንዲት ስህተት ብታገኝበት
እዚህ ሰፈር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነው
የምባረረው። የሰውን አመኔታ ላለመብላት
ጥንቃቄ እያደረግሁኝ እጓዛለሁ።

★ የፊንቴክ ባለቤት አቶ ዳንኤል ራሱ ደውሎልኝ
ሰዎች ለአውንታ 20 ሚሊዮን ብር እንስጠውና
ይኼንን ጉዳይ ያቁም ብለውኛል። ልስጣቸው ወይ?
ወይስ አንተ ተነጋግረህ ነው ወይ ብሎኛል።

★ ሕዝቡ የሚሰጠኝን 5 ብር ጣፍጦኝ ነው የምበላው።

★ መስሪያ ቤቴ ከሚሰጠኝ ደመወዝ በላይ
5 ብሯ ትጠቅመኛለች።

★ ለልጆቼ የማስተላልፈው ርስት ይኼ ብቻ ነው።

★ ይኼንን ንፁህነቴን ረሃብ ካላስቸገረኝ ፣ ድህነት
ካላስቸገረኝ ይዤው እጓዛለሁ።

★ ተደብድቤ ጳውሎስ ሆስፒታል ተኝቼ አውቃለሁ።

በመጨረሻም የማመሰግናቸው ፦

★ ለፌዴራል ፖሊስ ኢንስፔክተር ሀብታሙ
ላንተ ልዩ ክብር አለኝ።

★ ኮሚሽነር ብርሃኑ ኢትዮጵያዊነትን የምወደው
እንዳንተ ያሉ ሰዎች ስላሉ ነው እንጂ ተሟጦ
ባለቀ ነበር። ምልክቶቼ ትሆናላችሁ።
እጅግ አድርጌ አመሰግናለሁ።
በተጨማሪም ፦
ደመወዝ ከፋዮቼንም አመሰግናለሁ። እንዳትረሱ
ደመወዜን ክፈሉ ‼️"

ወይ መንሱር ጀማል
30/03/2026

ወይ መንሱር ጀማል

5637 likes, 266 comments. “ማሽቃበልጥ ግዴታ አይደለም”

ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ለቲክቶከር አዶናይ ያስተላለፈው መልዕክት 👇👇👇"ለአስተዋይ ቁጣና ተግሳጽ ሽልማት ነው‼️" (በድሉ ዋቅጅራ)"ሰግጥና ፈምስ!" የሚለውን ሳይሆን÷ አሁን ይህን አዶናይ ይዛች...
25/03/2026

ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ለቲክቶከር አዶናይ ያስተላለፈው መልዕክት
👇👇👇

"ለአስተዋይ ቁጣና ተግሳጽ ሽልማት ነው‼️" (በድሉ ዋቅጅራ)

"ሰግጥና ፈምስ!" የሚለውን ሳይሆን÷ አሁን ይህን አዶናይ ይዛችሁ አይደለም በኢትዮጵያ በዓለም ብትዞሩ ደስታው የእኔም ነው።
በርታ አዶናይ‼️

14/03/2026

❤❤❤

Address

Debre Zeyit

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mareko media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Mareko media:

Share