Dawuro Times

Dawuro Times አዳዲስ እና ጠቃሚ መረጃዎች DT

"በአንድ ቦክስ አህያውን ገድያለሁ"👉አቶ አባይነህ አበራ🙄።።።።።።በEBSTV ሰይፉ ፋንታሁን ሾው ላይ ቀርቦ "በአንድ ቦክስ አህያን ገድያለሁ" ብሎ የተናገረው። ባለ እረጅም ፊት ባለበት አባ...
16/05/2026

"በአንድ ቦክስ አህያውን ገድያለሁ"👉አቶ አባይነህ አበራ🙄
።።።።።።
በEBSTV ሰይፉ ፋንታሁን ሾው ላይ ቀርቦ "በአንድ ቦክስ አህያን ገድያለሁ" ብሎ የተናገረው። ባለ እረጅም ፊት ባለበት አባይነህ አበራ(አባው)። ከፈጣሪ ልዩ ተፈጥሮን የተቸረው አባይነህ አበራ(አባው) ተወልዶ ያደገው በደቡብ ምዕራብ ክልል በዳውሮ ዞን ነው።

ሰይፉ ፋንታሁን ሾው ላይ የAfrica Genus Record ላይ "እረጅም ፊት" ባለበትነት ወረቀት ተቀብሏል።

አባይነህ ለዳውሮ ህዝብ ልዩ ምልክት ነው።

🇪🇹

ኦማቴ ሚዲያ

ተወዳጁ የቦንጋ ከተማ ወጣት አረፈ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ ነዋሪ የነበረው ወጣት ጅሀድ በርታ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ​ጅሀድ በአካ...
13/05/2026

ተወዳጁ የቦንጋ ከተማ ወጣት አረፈ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ ነዋሪ የነበረው ወጣት ጅሀድ በርታ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

​ጅሀድ በአካባቢዉ እጅግ ተወዳጅ፣ ሰው አክባሪ፣ ተጫዋች እና ለሁሉ ቀና የሆነ መልካም ስብዕና የነበረው ወጣት ነበር። ጅሃድ በአከባቢው በሚካሄዱ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ባለው ንቁ ተሳትፎ ይታወቅ ነበር።

እየመጣ ነዉ ........💪
11/05/2026

እየመጣ ነዉ ........💪

ብልጽግና ፓርቲን የማይመርጥ አለ አሁን?
11/05/2026

ብልጽግና ፓርቲን የማይመርጥ አለ አሁን?

10/05/2026
በነገራችን ላይ ማንኛውም ቤሃሪ ማነኛውም ወገን ማነኛውም ክልል ይሄንን ድንካ መጠቀም ይችላል መስራት ይችላል።ነገር ግን በዚህ ድንኬ የመጀመርያ ይዞታ የድንካ መስራች የድንካ ባለቤት  #ዳዉሮ...
10/05/2026

በነገራችን ላይ ማንኛውም ቤሃሪ ማነኛውም ወገን ማነኛውም ክልል ይሄንን ድንካ መጠቀም ይችላል መስራት ይችላል።ነገር ግን በዚህ ድንኬ የመጀመርያ ይዞታ የድንካ መስራች የድንካ ባለቤት #ዳዉሮ ና #ዳዉሮ ብቻ ነው።💪💪ስለዚህ ይሄን በአለም ደረጃ በእርዝማኔው አቻ ያልተገኘለት የትንፋሽ መሳርያ ድንካ ባለቤት ዳዉሮ መሆኑ ሁልግዜ ልታወስ ይገባሌ።💪

መሌ ሆይ ስንወድህ በምክንያት ነው ሲጠሉህም በምክንያት! ሼር ሼር ሼርእኛ የምንወድህ በምክንያት ነበር፤ እነዛ የሚጠሉህም በጥላቻቸው ውስጥ ምክንያት ነበራቸው። ዛሬ ግን የሚገርመው ነገር የሚ...
10/05/2026

መሌ ሆይ ስንወድህ በምክንያት ነው ሲጠሉህም በምክንያት! ሼር ሼር ሼር
እኛ የምንወድህ በምክንያት ነበር፤ እነዛ የሚጠሉህም በጥላቻቸው ውስጥ ምክንያት ነበራቸው። ዛሬ ግን የሚገርመው ነገር የሚወዱህም የሚጠሉህም በአንድ የጋራ ህመም ፤ ቁስለት ውስጥ መገናኘታቸው ነው። በወቅቱ አንተን መቃወም የቻሉት፣ አንተን መጥላት የቻሉት፣ አንተን መተቸት የቻሉት ቢያንስ ትንፋሽ የሚሰጥ "ሀገር" ስለነበረቻቸው ነበር። ዛሬ ግን ጥላቻቸው በቁጭት ተተክቷል፤ እየጠሉህ ትናፍቃቸዋለህ፣ እየሰደቡህ ያደንቁሀል፤ ምክንያቱም ያንተ መኖር ለጠላቶችህም ጭምር ዋስትና ነበርና!*****
መሌ ሆይ ባንተ ዘመን እኮ*****
ኢትዮጵያ የሁላችን መጠለያ ነበረች። በሰቀቀን ፈርቶ የሚኖር፣ በክልሉ ታጥሮ የሚሰቃይ ዜጋ አልነበረም። ሰው በፈለገው ሰዓት፣ በፈለገው አቅጣጫ ይነግዳል። ማንም መንገድ ላይ አስቁሞ አያግደውም፣ ማንም በማንነቱ አያርደውም። ያኔ "ሀገር" የምትባል ታላቅ ጥላ ነበረችን። ዛሬ ግን ያ ጥላ ተነስቶብናል፤ ዛሬ ሀገሪቱ በሙሉ "አባት አልባ" ሆና የመፍረስ ዋዜማ ላይ ነች።*****
መሌ ሆይ አንድ ነገር ልጨምርልህ****
ሰላም በየቤታችን የለም። በየቀኑ የሚሰማው ጥይት፣ የሚታየው ጦርነት፣ የሚነገረው ስደት እና የሚቆጠረው ሬሳ መለያችን ሆኗል። በአማራ ፤ በትግራይ ፤ በአፋር ፤ በኦሮሚያ ፤ በደቡብ ብዙ ክልሎች ያለው ነገር ያስጠላል። ይሄን ስልህ ግን አዲስ አበባን እንደ ሌላው ክልል ታምሳለች ብዪ አልልህም አዲስ አበባ ሌላ ሀገር ሆናለች።*****
አዎ! አዲስ አበባ ተቀይራለች። መንገዱ፣ ፎቁ፣ መብራቱ፣ ፓርኩ በአይን ሲታይ የሆነ የአውሮፓ ከተማ መስላለች። ግን ምን ያደርጋል። መሌ ሆይ ያ በራሱ እንዲተማመን አድርገህ የገነባኸው ህዝብ ፊቱ ጠቁሯል፣ ቆዳው ገርጥቷል፣ ልቡ በጭንቀት ደምቷል። ቆንጆ ፎቆች መካከል ቆመው የሚጨነቁ የሚፈሩ ብዙ ዜጎችን አየን። ሰላም በሌለበት ፎቅ፣ ተስፋ በሌለበት መብራት ምን ይደረጋል? ህዝቡ ቆንጆ ከተማ ውስጥ ሆኖ "መቼ ነው የምሞተው?" ብሎ የሚጠብቅበት ዘመን ላይ ደርሰናል።****
የብዙዎች አባት መሌ ሆይ****
ህዝቡ ዛሬ ከምንም በላይ ውስጡ ይጮኻል። ያስብሀል፤ ያንተን አርቆ አሳቢነትህን ብልህነትህ የጎደለው ዛሬ ነው፣ ራእይህ የተራቆተው ዛሬ ነው። አንተን ስናስብ አይናችን በእንባ ይሞላል፤ ምክንያቱም ዛሬ የምናየው ብልጭልጭ ውበት ሳይሆን፣ በውስጡ የታመቀውን የህዝብህን ሲቃ ነውና። የሚፈራ ህዝብ በብልጭልጭ ነገር ይደሰታል ብሎ ማሰብ ከንቱ ነው።

ጌታቸው ረዳ ስለ ህወሓት።የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትና የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ ሕወሃት አሁን የያዘው መንገድ "የግዴለሽነት ቁማር" ነው በማለት አ...
10/05/2026

ጌታቸው ረዳ ስለ ህወሓት።

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትና የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ ሕወሃት አሁን የያዘው መንገድ "የግዴለሽነት ቁማር" ነው በማለት አፍሪካ ሪፖርት መጽሄት ላይ ዛሬ ባወጡት አዲስ መጣጥፍ ተቹ።

ጌታቸው፣ ሕወሃት ከኤርትራ መንግሥትና ሌሎች የአገር ውስጥ ቡድኖች ጋር ስልታዊ አጋርነት ፈጥሮ በሠራው ስሌት "የልብ ልብ ተሠምቶታል" ብለዋል።

የሕወሃት አመራር ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ውጥረቶችን በማባባስ የፈለኩትን አገኛለሁ የሚል አደገኛ ስሌት ይዟል ሲሉ የተቹት ጌታቸው፣ ትግራይ አኹን ለደረሠችበት ቀውስ እርሳቸው ጭምር ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ጌታቸው የሕወሃት አመራር ቡድናዊ ጥቅሙን ከትግራይ ሕዝብ ጥቅም ጋር አብሮ ጨፍልቆ ማቅረቡ እጅግ አደገኛው ክስተት መኾኑንም በመጣጥፋቸው ላይ አስፍረዋል።

Address

Bole
1000

Telephone

+251917922665

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawuro Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share