ኬቲኤ ቤተሰብ KTA Bieteseb

ኬቲኤ ቤተሰብ KTA Bieteseb This page used to share videos that are produced by me, and videos that are very fun and important

" የፖሊስ ደንብ አልባሳትን አስመስሎ መጠቀም ፍፁም ክልክል ነው "‼️🗣የአዲስ አበባ ፖሊስየአዲስ አበባ ፖሊስ ነባሩን በመተካት ሥራ ላይ ያዋላቸውን ሦስት ዓይነት የደንብ አልባሳትን አስመስሎ...
13/11/2021

" የፖሊስ ደንብ አልባሳትን አስመስሎ መጠቀም ፍፁም ክልክል ነው "‼️

🗣የአዲስ አበባ ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ነባሩን በመተካት ሥራ ላይ ያዋላቸውን ሦስት ዓይነት የደንብ አልባሳትን አስመስሎ መጠቀም ፍፁም ክልክል መሆኑን አስታውቋል፡፡

በአገር አቀፍ ደረጃ የፖሊስ ተቋማትን ለማዘመን በተያዘው ስትራቴጂካዊ እቅድ የፖሊስ ሠራዊት አርማ እና የደንብ ልብስ እንዲቀየር በተወሰነው መሰረት የአዲስ አበባ ፖሊስ አዲስ አርማና የደንብ ልብስ ስራ ላይ ማዋሉ ይታወቃል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ነባሩን የደንብ ልብስ በሦስት ልዩ ልዩ ዩኒፎርሞች ተክቷል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኦሞ ሸሚዝ በጥቁር ሰማያዊ ሱሪ ከነ መለዮው፣ ካኪ ሱሪ እና ሸሚዝ በቦኔት መለዮ የደንብ ልብስን ለመደበኛ የፖሊስ ስራ እንዲሁም ቡራቡሬ ወይም ሬንጀር መልክ ያለው ለቋሚና ተወርዋሪ ኃይል የሚጠቀም መሆኑን ገልጿል።

አዲስ ስራ ላይ የዋለውን ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደነገገ ስለሆነ ከአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ፖሊስ አሳስቧል።

የአ/አ ፖሊስ ከዚህ ቀደም ሲጠቀምበት የነበረው ነባሩ የደንብ ልብስ አገልግሎት የማይሰጥ መሆኑ ከዚህ በፊት መገለፁ ይታወሳል።

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

This is አብርሽ ፳፩ Abrsh 21 Channel. My name is Abraham Mare and I have created this channel to share helpful or Entertaining videos about New Amharic Movie, Vi...

በባሕር ዳር ከተማ ግሸ አባይ ክፍለ ከተማ በአንድ ግለሰብ ቤት ከ3 ሺህ በላይ ጥይትና ሌሎች የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ባሕር ዳር፡ ሕዳር 04/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ...
13/11/2021

በባሕር ዳር ከተማ ግሸ አባይ ክፍለ ከተማ በአንድ ግለሰብ ቤት ከ3 ሺህ በላይ ጥይትና ሌሎች የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

ባሕር ዳር፡ ሕዳር 04/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ2ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ በከተማ አስተዳደሩ ግሽ አባይ ክፍለ ከተማ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ተከማችቶ የተገኘ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል፡፡

የ2ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ኀላፊ ምክትል ኮማንደር ጌትነት አበበ እንደገለጹት ጥቆማው የደረሰው ከማኅበረሰቡ ነው፡፡ በጥቆማው መሰረት ተጠርጣሪው ቤት ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ፍተሻ በማካሄድ በግለሰቡ መኖሪያ ውስጥ ሁለት ክላሽ፣ ከ3 ሺህ በላይ የክላሽ እና የብሬን ጥይት፣ አንድ ኤፍዋን ቦንብ እና አንድ ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ በቁጥጥር መዋሉን ለአሚኮ ተናግረዋል፡፡

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደ እንደሆነም ምክትል ኮማንደሩ አስረድተዋል፡፡

የቤት አከራዮች የተከራዮቻቸውን ማንነት በአግባቡ በማጣራት አድራሻቸውን ለፖሊስ እንዲያሳውቁም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርተው በሚገኙ አካት ላይ ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ ፖሊስ ከፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝም ምክትል ኮማንደር ጌትነት ጠቁመዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ነዋሪ በተለይም ወጣቱ ለወቅታዊ ጉዳይ ትኩረት በመስጠት ከጸጥታ ኃይሉ ጋር እያደረጉት ያለው የቅንጅት ሥራ የሚበረታታ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
©አሚኮ
ዘጋቢ፡- ደጀን አምባቸው

አካባቢዎን በንቃት ይጠብቁ!
ለጸጥታ ስጋት የሆኑ ጉዳዮችን ሲመለከቱ ለጸጥታ ኃይሎች ያሳውቁ!

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

ኢሰመኮ ከሐምሌ ወር 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል በሕወሓት ኃይሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብትና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶችን በተመለከተ ያደረገውን ምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆኗል።ከሰኔ 21 - ...
13/11/2021

ኢሰመኮ ከሐምሌ ወር 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል በሕወሓት ኃይሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብትና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶችን በተመለከተ ያደረገውን ምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆኗል።

ከሰኔ 21 - ነሃሴ 22 /2013 ዓ/ም ያለውን ጊዜ የሚሸፍነው ይህ ሪፖርት እስከ ነሃሴ 30/ 2013 ድረስ የተካሄደ ምርመራ ውጤት ሲሆን የምርመራ ቡድኑ 128 ቃለመጠይቆችን፣ ከተጎጂዎችና ቤተሰቦቻቸው፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች፣ የሲቪልና የፀጥታ አካላት፣ ከሲቪክ ማኅበረሰብ አባላት፣ ከተራድዖ ድርጅቶች ጨምሮ 21 የቡድን ውይይቶችን አድርጓል።

በሪፖርቱ እንዳመላከተው ምርመራው ባተኮረባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች በተደረገው ጦርነት ቢያንስ የ184 ሲቪል ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ እንዲሁም በርካታ ሰዎች የአካል ጉዳት እና የሥነ ልቦና ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በተለይ የሕወሓት ታጣቂዎች በቁጥጥራቸው ስር በገቡ ከተሞች እና ገጠራማ አካባቢዎች ሲቪል ሰዎችን ተኩሰው መግደላቸውንና ማቁሰላቸውን፣ ሰፊ የንብረት ዘረፋ እና ውድመት ሆን ብለው መፈፀማቸውን ኢሰመኮ አረጋግጧል።

እንዲሁም የሕወሓት ኃይሎች ወደ ከተሞች ከባድ መሳሪያዎችን መተኮሳቸውን፤ በሲቪል ሰዎች መኖሪያ ቤቶችና ቅጥር ግቢዎች ውስጥ ምሽግ በመቆፈር እና ከባድ መሳሪያዎችን በመተኮስ ሲቪል ዜጎችን በአፀፋ ለሚተኮሱ ከባድ መሳሪያዎች ጥቃት ማጋለጣቸውን፤ በዚህ የበርካታ ሲቪል ሰዎች ሞትና አካል ጉዳት እንዲከሰት እንዲሁም ንብረት እንዲወድም ምክንያት መሆናቸውን ሪፖርቱ ያሳያል።

በሌላ በኩል የመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት ታጣቂዎች ሲቪል ሰዎች የሚኖሩባቸው መንደሮች ውስጥ ሆነው የሚፈፅሙበትን ጥቃት ለመከላከል እና ለማጥቃት ከባድ መሳሪያዎችን በመጠቀሙ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞትና አካል ጉዳት ደርሷል፤ ንብረት እንዲወድም ሆኗል።

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_coEthiopia Bietachin ኢትዮጵያ ቤታችንk.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

በአሶሳ ከተማ ፖሊስ በአንድ ግለሰብ ቤት ባደረገው ድንገተኛ ፍተሸ ጂ ፒ ኤስን ጨምሮ አደንዛዥ እጽ፣ የተለያዩ የባንክ ደብተሮች፣ ፓስፖርቶችና መታወቂያዎችን  ተገኝተውበታል። የአሶሳ ከተማ አ...
12/11/2021

በአሶሳ ከተማ ፖሊስ በአንድ ግለሰብ ቤት ባደረገው ድንገተኛ ፍተሸ ጂ ፒ ኤስን ጨምሮ አደንዛዥ እጽ፣ የተለያዩ የባንክ ደብተሮች፣ ፓስፖርቶችና መታወቂያዎችን ተገኝተውበታል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ኢንስፔክተር ደረጃ ኢታና እንደገለጹት፣ በከተማው 8 ማዳበሪያ ካናቢስ መሠል አደንዛዥ እጽ በመደበቅ ለሽብር ተግባር ሊያውል የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ፖሊስ ትናንት በአንድ ግለሰብ ቤት በካሄደው ድንገተኛ ፍተሻ ጂ ፒ ኤስን ጨምሮ፣ 200 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እጽ፣ ጥሬ ገንዘብ፣ በርካታ የባንክ ደብተሮችና በተለያዩ ግለሰቦች ስም የተመዘገቡ የተለያዩ ከተሞች መታወቂያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ግለሰቡ በሚሰራበት ሱቅ ውስጥ በተደረገ ፍተሸ ሁለት ማዳበሪያ አደንዛዥ እጽ መገኘቱን ጠቁመው፣ ክትትሉን በማጠናከር በመኖሪያ ቤቱ በተደረገ ፍተሸ ደግሞ ተጨማሪ ስድስት ማዳበሪያ አደንዛዥ እጽ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

በግለሰቡ በተከናወነ ተጨማሪ ፍተሸ ደግሞ የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ገንዘቦች፣ በርካታ የባንክ ደብተሮች፣ የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን መታወቂያዎች፣ ጂ ፒ ኤስ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ተገኝተው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል፡፡

ከግለሰቡ የተያዘው አደንዛዥ እጽ ከአዲስ አበባ የመጣ እና ወደ ሸርቆሌ ወረዳ ጉኑ ቀበሌ ሊላክ እንደነበርና ህጻናትና ወጣቶችን በማደንዘዝ ወደአላስፈላጊ ድርጊት ለማሠማራት የታሰበ እንደነበር ኢንስፔክተር ደረጀ ገልጸዋል፡፡

በግለሰቡ ቤት በተደረገ ፍተሸ የተያዙ ንብረቶች
1. 200 ኪሎ ግራም አደንዛዥ እጽ
2. 160 ሺህ ብር ጥሬ ገንዘብ
3. 3 ባለሃምሳ የሱዳን ፓውንድ
4. 1 ትንሽ ጋርሚን ጂ ፒ ኤስ ከነ ማንዋሉ
5. 1 ትልቅ ጋርሚን ጂ ፒ ኤስ ከነ ማንዋሉ
6. 2 የጂ ፒ ኤስ ሲዲ ማንዋል
7. 1 ትንሽ ሶኒ ፎቶ ካሜራ
8. 1 ቴክኖ ስክርን ተች የሞባይል ቀፎ
9. አንድ ጃኖራ ትንሽ ሞባይል
10. ሁለትና አራት ቻርጅ ማድረጊያ መሠል ቁሳቁስ
11. የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡክ እና በውስጡ 6 ሺህ 328 ብር ከ 60 ሳንቲም ያለው
12. የወጋገን ባንክ እና 1 ሺህ 270 ብር ከ93 ሳንቲም ያለው
13. አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ እና በውስጡ 278 ሺህ ብር ከ24 ሳንቲም የያዘ
14. አቢሲንያ ባንክ ቡክ እና 196 ብር ከ50 ሳንቲም ያለው
15. የብድርና ቁጠባ መታወቂያ ደብተር
16. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 10 የነዋሪዎች መታወቂያ በናሆም ተከስተ ረዳ ስም የተመዘገበ
17. የደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ መታወቂያ ደብተር በገብረ ስላሴ ገ/ክርስቶስ ስም የተመዘገበ
18. የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የ04 ቀበሌ ጸጋ ገብረ-ህይወት ስም የተመዘገበ መታወቂያ
19. የመድኃኔዓለም መረዳጃ በገብረ-ስላሴ ገ/ክርስቶስ ስም የተመዘገበ የአባልነት መታወቂያ
20. የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የ04 ቀበሌ የነዋሪዎች ስኳርና ዘይት ማከፋፈያ ገብረ-ህይወት ስም የተመዘገበ መታወቂያ
21. የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ቀጠና አንድ የተመዘገበ የነዋሪዎች መታወቂያ
22. ማኅበር ልማት ትግራይ በገብረ-ስላሴ ገ/ክርስቶስ ስም የተመዘገበ
23. አንድ ትልቅ ጂ ፒ ኤስ
24. አንድ መካከለኛ ጂ ፒ ኤስ
25. አንድ ትልቅ ቻርጅ ማድረጊያ (ማቀጣጠያ
26. የኒያላ ጂጋራ እስቴካ በቁጥር 100
27. በአረብኛ የተጻፈ የደቡብ ሱዳን የባንክ ስቴትመንት
28. የደቡብ ሱዳን ቪዛ
በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢንስቴክተር ደረጀ ተናግረዋል፡፡

ፖሊስ በከተማው ያለውን የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ ህብረተሰቡ አካባቢውን በንቃት በመከታተል የተለዬ ሁኔታ ሲለከት ለፖሊስ በመጠቆም የጀመረውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘገባዉ የአሶሳ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነዉ::

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

ከትናንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ፌስቡክ፣ ሜሴንጀር፣ ኢንስታግራም እና የተወሰኑ የዋትስአፕ እና ቴሌግራም መገናኛ ዘዴዎች እንደማይሰሩ የሀገራትን ኢንተርኔት የሚከታተለው ኔትብሎክስ የተሰኘው ድርጅት...
09/11/2021

ከትናንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ፌስቡክ፣ ሜሴንጀር፣ ኢንስታግራም እና የተወሰኑ የዋትስአፕ እና ቴሌግራም መገናኛ ዘዴዎች እንደማይሰሩ የሀገራትን ኢንተርኔት የሚከታተለው ኔትብሎክስ የተሰኘው ድርጅት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል።

የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ አገልግሎት ያቋረጠው፣ ትናንት የተጀመረው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ወረቀት ተሰርቋል የሚሉ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ እንደሆነ ድርጅቱ ገልጧል። መንግሥት ግን ፈተናው ተሰርቆ ወጥቷል መባሉን አስተባብሏል።

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

This is አብርሽ ፳፩ Abrsh 21 Channel. My name is Abraham Mare and I have created this channel to share helpful or Entertaining videos about New Amharic Movie, Vi...

ካናዳዊ ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርስ ለኢትዮጵያዊያን የላከው መልዕክት‼️በኢትዮጵያ ላይ የተቃጡ የውጪ ዘመቻዎችን በመመከት የኢትዮጵያ ወዳጅ እንደሆነ የሚታወቀው ካናዳዊ ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርስ ኢትዮጵያዊያን...
08/11/2021

ካናዳዊ ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርስ ለኢትዮጵያዊያን የላከው መልዕክት‼️

በኢትዮጵያ ላይ የተቃጡ የውጪ ዘመቻዎችን በመመከት የኢትዮጵያ ወዳጅ እንደሆነ የሚታወቀው ካናዳዊ ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርስ ኢትዮጵያዊያን የሃገራቸውን እውነታ ለማስረዳት ድምፃቸውን በጋራ እንዲያሰሙ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

ለሃገራችሁ ክብርና ነጻነት በጋራ በቆማችሁበት በዚህ ወቅት አብሬአችሁ ብሆን ደስታዬ ነበር፡፡

አጠገባችሁ ባልገኝም እኔን ጨምሮ ምዕራባዊያን እና የተባባሩት መንግስታት በናንተ ላይ የሚፈጥሩትን ጫነሳ እና ጣልቃ ገብነት የሚቃወሙ በርካታ ወንድሞች እና እህቶች እዚህ ካናዳ፣ አሜሪካና አውሮፓ እንዳሉ ልነግራችሁ እወዳለሁ፡፡

ቤተሰቦቻችሁ እና ጓደኞቻችሁ ለሃገራቸው መስዋዕት ለመክፈል ወደ ጦር ግንባር ሲሄዱ ማየት ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ በአሸባሪው ቡድን የተገደሉ ወገኖች በየቦታው ወድቀው ማየት እጅግ ያማል፡፡

ነገር ግን ምርጫ የለም፡፡
እነሱ እድል ካገኙ እናንተን ሊያጠፉ መሆኑን ታውቃላችሁ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ የምዕራባዊያን መንግስታት አሸባሪው ቡድን እንዲገላችሁ እንደፈቀዱለት ግልፅ ሆኗል፡፡
ስለዚህ ነጻነታችሁን ለማረጋገጥ ዋጋ መክፈል አለባችሁ፡፡ አያት ቅድመ አያቶቻችሁ በነፃነት እንድትኖሩ የከፈሉትን ዋጋ እናንተም ደግማችሁ ነጻነታችሁን አረጋግጡ፣ ራሳችሁን ከዚህ ገዳይ ቡድን አድኑ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ምዕራባዊያን እውነቱን ክደው ፊታቸውን ቢያዞሩባችሁም ሌሎች እውነቱን ተረድተው ለማሳወቅ የሚጥሩ ወገኖቻችሁ ከጎናችሁ መሆናቸውን መግለፅ እፈልጋለሁ፡፡

እናንተ ኢትዮጵያ ናችሁ! በዓለም ላይ ብቸኛው የሰው ዘር መገኛ ምድር! አሁንም በከፍታ ላይ ያላችሁ፡፡ ስለዚህ በዚህ ጊዜ ባህር አቋርጦ ዋሺንግተን፣ ጀኔቫ፣ ብራስልስ እና ግብፅ ድረስ ሊሰማ የሚችል ድምጻችሁን በጋራና በአንድነት በማሰማት የሃገራችሁን እውነታ አሳውቁ፡፡

ድምፃችሁ እንዲሰማ አድርጉ!
ጫናዎቹን መቋቋም ትችላላችሁ!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች!”
(ጄፍ ፒርስ)
Esat Tv

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

This is አብርሽ ፳፩ Abrsh 21 Channel. My name is Abraham Mare and I have created this channel to share helpful or Entertaining videos about New Amharic Movie, Vi...

የገበሬዎች ጀብዱ በከሚሴ‼️👉🏿 35 ማርከው መሳሪያውን ታጥቀዋል።👉🏿 ከ35 ውስጥ 15ቱ የህወሓት ወታደሮስ ሲሆኑ እርምጃ ወስደውባቸዋል።👉🏿 ቀሪ 20ዎቹ ከመከላከያ በግዳጅ ጁንታው ያሰማራቸው...
08/11/2021

የገበሬዎች ጀብዱ በከሚሴ‼️
👉🏿 35 ማርከው መሳሪያውን ታጥቀዋል።
👉🏿 ከ35 ውስጥ 15ቱ የህወሓት ወታደሮስ ሲሆኑ እርምጃ ወስደውባቸዋል።
👉🏿 ቀሪ 20ዎቹ ከመከላከያ በግዳጅ ጁንታው ያሰማራቸው ነበሩ። ገበሬዎቹ ለመከላከያ አስረክበል።
ከመከላከያ ተማርከው ከሕወሓት ጋር የተሰለፉ 20 ወታደሮች በከሚሴ ግንባር በገበሬ ሚሊሻዎች ተማረኩ። ገበሬዎቹ ደፈጣ ጥለው ወደ 35 ወታደሮችን የማረኩ ሲሆን ከእነዚህ 15 የሕወሐት ወታደሮች በመሆናቸው መተዋቸዋል። ቀሪዎቹና ከመከላከያ ተማርከው በግድ የተሠማሩትን ወታደሮች ደግሞ ማርከው ለመከላከያ አስረክበዋቸዋል። የ35ቱን መሣሪያ ወስደው ገበሬዎቹ ታጥቀዋል።

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

This is አብርሽ ፳፩ Abrsh 21 Channel. My name is Abraham Mare and I have created this channel to share helpful or Entertaining videos about New Amharic Movie, Vi...

ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ኮማንድ ፖስት የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት‼️1ኛ. ከዛሬ ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 5 ማለትም ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት አምስት የስራ ቀናት በ...
08/11/2021

ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ኮማንድ ፖስት የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት‼️

1ኛ. ከዛሬ ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 5 ማለትም ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት አምስት የስራ ቀናት በባህርዳር ከተማ የሚገኝ ያልተመዘገበ ማንኛውም የግል የጦር መሳሪያ በአካባቢያችሁ በሚገኝ ሚሊሻ ጽ/ቤት በአምስት ቀናት ውስጥ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን።

2ኛ. በጦር ግንባር በነበረ ዘመቻ ላይ ማንኛውንም የጦር መሳሪያና ትጥቅ ይዛችሁ ወደ ከተማ ለተመለሳችሁ፦

ግንባር የመሄድ ፍላጎት ያላችሁ መንግስት ባወጣው አደረጃጀት ታቅፋችሁ ወደ ግንባር እንድትሄዱ እናሳስባለን።
ከፀጥታ ሃይሉ ውጭ መሳሪያ ይዞ በከተማችን በተለያዩ ስፍራዎች ሲንቀሳቀስ የተገኘ ማንኛውም አካል በፀጥታ ሃይሉ ተጠያቂ መሆኑን እናሳስባለን።

3ኛ. በፋኖ አደረጃጀት ለሰለጠነ ማንኛውም የታጠቀ ሃይል፦

በፋኖ አደረጃጀት ሰልጥናችሁ ወደ ግንባር የመሄድ ፍላጎት ያላችሁ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ገብታችሁ እንድትዘምቱ እያሳሰብን ከተማ አስተዳደሩ ማንኛውንም የሎጅስቲክ ድጋፍ የምናቀርብ መሆኑን እንገልፃለን።

በፀጥታ ምክር ቤቱ ወይም በሰላምና ደህንነት ቢሮ ስምሪት ሳይቀበል መሳሪያ ታጥቆ በከተማችን በተለያዩ ስፍራዎች የጦር መሳሪያ ይዞ ሲንቀሳቀስ የተገኘ በፀጥታ ሃይሉ ተጠያቂ መሆኑን እናሳስባለን።

4ኛ. ከተለያዩ የጦርነት ቀጠናዎች ተፈናቅለው ወደ ከተማችን ባህርዳር ስለ መጡ ግለሰቦች፦

ተፈናቃዮቹ ለተፈናቃይ በተዘጋጀው መጠለያ ካንፕ እየተመዘገቡ እንዲገቡ እያሳሰብን። ይህ ካልሆነ ደግሞ ማንኛውም ቤት አከራይ የተከራይ ግለሰቦችን መታወቂ ኮፒ በማድረግ በአካባቢው ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ እንዲያሳውቅ እናሳስባለን።

ይህም የሚሆንበት ምክኒያት በተፈናቃይ ስም ሰርጎ ገቦች እንዳሉ ስለተደረሰበት ለከተማችን ደህንነት ነው።

#ማሳሰቢያ፦

ከላይ የተዘረዘሩትን ሀሳቦች በአምስት ቀን ውስጥ ተግባራዊ በማያደርግ ግለሰብ ላይ መንግስት ህጋዊ ርምጃ እንደሚወስድ ስንገልፅ ከአክብሮት ጋር ነው።

©የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፀጥታ ምክር ቤት (ኮማንድ ፖስት)

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

This is አብርሽ ፳፩ Abrsh 21 Channel. My name is Abraham Mare and I have created this channel to share helpful or Entertaining videos about New Amharic Movie, Vi...

08/11/2021
የ12ኛ ክፍል ፈተና መሰጠት ተጀመረ።የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከዛሬ ጥቅምት 29 ጀምሮ መሰጠት ተጀምሯል።ፈተናው ኅዳር 02/2014 ዓ.ም ይጠናቀቃል።በዛሬ ጥዋት የፈተና መርሃ ግብር መሰረ...
08/11/2021

የ12ኛ ክፍል ፈተና መሰጠት ተጀመረ።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከዛሬ ጥቅምት 29 ጀምሮ መሰጠት ተጀምሯል።

ፈተናው ኅዳር 02/2014 ዓ.ም ይጠናቀቃል።

በዛሬ ጥዋት የፈተና መርሃ ግብር መሰረት የእንግሊዘኛ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል።

በጸጥታ ችግር ምክንያት በመጀመሪያው ዙር ፈተናው በማይሰጥባቸው አካባቢዎች ፈተናው በሁለተኛ ዙር ለመስጠት እቅድ ተይዟል።

በ131 የፈተና ጣቢያዎች በጠቅላላው 36 ሺህ 340 ተማሪዎች ለብሔራዊ ፈተናው በመጀመሪያ ዙር አይቀመጡም።

ዛሬ ለሀገር አቀፍ ፈተና የተቀመጡ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ፈተና እንዲሆን እየተመኘን ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ከፈተናው ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች እንድትጠነቀቁ አደራ እንላለን::

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ከሰሞኑ የተወሰኑ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፦- የተዛቡ፣- ትክክለኛ የጋዜጠኝነት መርህን ያልተከተሉ፣ - የአገር ሉዓላዊነትና የህዝቦችን አንድነት አደ...
08/11/2021

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ከሰሞኑ የተወሰኑ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፦
- የተዛቡ፣
- ትክክለኛ የጋዜጠኝነት መርህን ያልተከተሉ፣
- የአገር ሉዓላዊነትና የህዝቦችን አንድነት አደጋ ውስጥ የሚጥሉ ብሎም የፖለቲካዊ ውግንና ያላቸውን ዘገባዎች ማሰራጨታቸውን አጥብቆ ኮነነ።

ማህበሩ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ የሰሩትን ዘገባ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህ መግለጫው ሰሞኑን አዲስ አበባን እና ዙሪያዋን በተመለከተ የተሰራጩ ዘገባዎችን ትክክለኛነትና ሚዛናዊነት ለማጣራት ጥረት ማድረጉን ገልጿል።

ለዘገባ ከተንቀሳቀሱና በየአካባቢው ከሚኖሩ አባሎቹ ብሎም ከነዋሪዎች ባገኘነው መረጃ መሰረት እስካሁን ድረስ አዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙት አካባቢዎች ሁሉ በተለመደው እንቅስቃሴያቸው ላይ ይገኛሉ ብሏል።

ማህበሩ ከሰሞኑ ዓለምአቀፍ ሚዲያዎች የተዛቡ እና ፖለቲካዊ ውግንና ያላቸውን ዘገባዎች ማሰራጨታቸውን አጥብቆ የኮነነ ሲሆን በእንደዚህ ያሉ ሙያዊ መርሆን ባልተከተሉ ዘገባዎች እየተሳተፉ ያሉ ጋዜጠኞች ጋዜጠኝነታቸውን በሙያዊ አስተምህሮው መሰረት እንዲፈፅሙ ጠይቋል።

በተጨማሪ መቀመጫቸውን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ያደረጉና ስለኢትዮጵያ የሚዘግቡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ባለሙያዎች ከእንደዚህ አይነት አዘጋገብ እንዲወጡ አጥብቆ አሳስቧል።

የኢትዮጵያ መንግስትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትም የየትኛውም መገናኛ ብዙኃን ዘጋቢዎች ተገቢውን መረጃ እንዲያገኙና በተለያዩ አካባቢዎች ተዘዋውረው እውነተኛ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ እንዲችሉ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስቧል።

የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃንም ፈጣን፣ ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ሚዛናዊ መረጃዎችን እንዲያቀርቡ መክሯል።

*ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
════❁✿❁ ════
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️

YouTube:-https://www.youtube.com/channel/UC5CVRtNWiq0JlisEFIiQaiA?sub_confirmation=1
Facebook:- https://m.facebook.com/EthiopiaBietachin/
Instagram: - https://www.instagram.com/abrsh_021/
Telegram:- https://t.me/ethiopiabietachin
Twitter:-https://twitter.com/Abrsh211

Address

Bahir Dar
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኬቲኤ ቤተሰብ KTA Bieteseb posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to ኬቲኤ ቤተሰብ KTA Bieteseb:

Shortcuts

Share