ጉድ አዲስ - Good Addis

ጉድ አዲስ - Good Addis Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጉድ አዲስ - Good Addis, Arts and entertainment, Addis Ababa.

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ወደ አዲስ እና እጅግ አደገኛ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የእስራኤል ጥቃት እየተጠናከረ ሲሄድ፣ ቢያንስ 20 የኢራን ከፍተኛ የጦር አዛዦች መገደላቸውን ሮይተርስ ዘ...
13/06/2025

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ወደ አዲስ እና እጅግ አደገኛ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የእስራኤል ጥቃት እየተጠናከረ ሲሄድ፣ ቢያንስ 20 የኢራን ከፍተኛ የጦር አዛዦች መገደላቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት (IDF) በኢራን የኑክሌር ፕሮግራም ልብ የሆነውን የናታንዝን የከርሰ-ምድር የኑክሌር ማዕከል መትቶ መውደሙን አስታውቋል። የኢራኑ ፕሬዝዳንት በበኩላቸው እስራኤል በፈጸመችው ድርጊት "እንድትጸጸት" የሚያደርግ ጠንካራ እና ህጋዊ ምላሽ እንደሚሰጡ ዝተዋል።

የእስራኤል ጥቃት በኢራን የጦር አመራር ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን መረጃዎች እያመለከቱ ነው። የ20 ከፍተኛ አዛዦች መገደል የኢራንን የኮማንድ እና የቁጥጥር መዋቅር በእጅጉ የሚጎዳ ሲሆን፣ ይህ ቁጥርም ሊጨምር እንደሚችል ስጋት አለ። ከዚህም በተጨማሪ የእስራኤል ጦር የጀመረው ወታደራዊ ዘመቻ በቀላሉ የሚቆም እንዳልሆነና ቢያንስ ለ14 ቀናት ሊቀጥል እንደሚችል አስታውቋል። ይህ ረጅም የጊዜ ገደብ ግጭቱ ወደ ሙሉ እና ቀጣይነት ያለው ጦርነት ሊያመራ ይችላል የሚለውን ስጋት አባብሶታል።

በጣም አስደንጋጩ መረጃ የእስራኤል ጦር በናታንዝ የሚገኘውን የኢራን የኑክሌር ማበልጸጊያ ማዕከል ኢላማ ማድረጉ ነው። ጦሩ በማዕከሉ ውስጥ የሚገኝ አንድ የከርሰ-ምድር ኮምፕሌክስ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት መመታቱን አረጋግጧል። ናታንዝ የኢራን የኑክሌር ፕሮግራም ዋና ማዕከል በመሆኑ፣ ይህ ጥቃት የእስራኤል አላማ የኢራንን የጦር ኃይል ማዳከም ብቻ ሳይሆን የኑክሌር አቅሟንም ሙሉ በሙሉ ማውደም መሆኑን በግልጽ ያሳያል።

የኢራን ምላሽም ጠንካራ ሆኗል። የኢራኑ ፕሬዝዳንት "ቴህራን በእስላማዊ ሪፐብሊክ ግዛት ላይ ለተፈጸመው ጥቃት የምትሰጠው ኃይለኛ እና ህጋዊ ምላሽ እስራኤል በሰራችው ነገር እንድትጸጸት ያደርጋታል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በሌላ በኩል የጥቃቱ ሰብዓዊ ጉዳትም እየታየ ነው። የቀይ ጨረቃ ማህበር ባወጣው ሪፖርት መሰረት በ12 የኢራን ግዛቶች በተፈጸመው የእስራኤል ጥቃት ቢያንስ 95 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ይህ የጥቃቱ ስፋት በአንድ አካባቢ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢራን ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ያሳያል። አለም አሁን ሁለቱ ሀገራት ወደማይመለሱበት መንገድ ከመግባታቸው በፊት ይህንን አደገኛ የእሳት ነበልባል ማን ያበርደው ይሆን በሚል በከፍተኛ ስጋት እየተመለከተ ነው።

የመሄጃ ብቻ የተቆረጠበት ትኬትየሶፍትዌር ባለሙያው ፕራቲክ ጆሺ ለንደን ውስጥ ለስድስት ዓመታት ኖሯል። ህንድ የሚኖሩትን ባለቤቱንና ሶስት ልጆቹን ወደ ለንደን አምጥቶ መኖር የሁልጊዜ ህልሙ ነ...
13/06/2025

የመሄጃ ብቻ የተቆረጠበት ትኬት

የሶፍትዌር ባለሙያው ፕራቲክ ጆሺ ለንደን ውስጥ ለስድስት ዓመታት ኖሯል።

ህንድ የሚኖሩትን ባለቤቱንና ሶስት ልጆቹን ወደ ለንደን አምጥቶ መኖር የሁልጊዜ ህልሙ ነበር።

ከስድስት ዓመታት ጥበቃ በኋላ ሕልሙ እውን ሆነ። ከሁለት ቀናት በፊት በኡዲፑር የምትኖረው እውቅ ሐኪም የሆነችውን ባለቤቱን ዶክተር ኮሚ ቪያስ ሥራዋን በፋቃደኝነት ለቀቀች። ሻንጣዎቹ ተዘጋጁ።

ትላንት ጠዋት ቤተሰብ በተስፋና በደስታ ተሞልቶ ሕንድ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር 171 ወደ ለንደን ለማምራት ጉዞአቸውን ከመጀመራቸው በፊት ይህንን ሰልፊ ተነስተው ለወዳጅ ለዘመዶቻቸው ላኩ። መመለሻን በሌለው የተቆረጠው የአንድ ጉዞ ታሪክ ህልማቸውን እውን እንዲሆን አላደረጋቸውም። አውሮፕላኑ ተከሰከሰ ።

በቅፅበት ሕልማቸው ወደ አመድነት ተለውጧል። የምትገነቡትን ሁሉ ፣ ተስፋ የምታደርጉትን ነገር ሁሉ ፣ የምትወዱትን ሁሉም ነገር በክር የተንጠለጠለ ነው።

ደስታን ለነገ ለመጀመር ብላችሁ አታስቀምጡ። ዛሬ ኑሩት።

ደግ አይለፋችሁ ❤️

እነዚህን ሁለት ፎቶዎች ተመልከቷቸውየመጀመርያው በወርሃ መስከረም 2019 ዓ.ም በኢንስታግራም ላይ የተፖሰተሁለተኛው ፎቶ ደግሞ በወርሃ ሰኔ 2021 ዓ.ም ኖርቪች ሆስፒታል ውስጥ የተነሳ ነውይ...
16/04/2025

እነዚህን ሁለት ፎቶዎች ተመልከቷቸው

የመጀመርያው በወርሃ መስከረም 2019 ዓ.ም በኢንስታግራም ላይ የተፖሰተ

ሁለተኛው ፎቶ ደግሞ በወርሃ ሰኔ 2021 ዓ.ም ኖርቪች ሆስፒታል ውስጥ የተነሳ ነው

ይህች ሴት ኔፓልን በመወከል በአለም የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ የአሸናፊነት ክብርን የተቀዳጀችው ኒሻ ጊሚሬ ነች

ከድሀ ቤተሰብ የተገኘችው እና ከልጅነቷ ጀምሮ የቁንጅና ተወዳዳሪ እና የፊልም ተዋንያን የመሆን ህልም የነበራት ሚስ ኒሻ ጊሚሬ በ2018 ዓ.ም በህንድ ፊልሞች ላይ መተወን ስትጀምር እና የተለያዩ ሞዴሊንግ ስራዎች በመስራት በድህነት ያሳደጏትን ቤተሰቦች የመካስ ተስፋን ሰነቀች

የፊልም አሰሪዎች ተረባረቡባት

የአልባሳት አምራቾች እንድታስተዋውቅላቸው ተማፀኗት

በኔፓል እና በህንድ የሚገኙ የመዝናኛ ድርጅቶች ለመኗት

በወርሃ ጥር 2019 ዓ.ም የሞዴሊንግ እና ትወና አድማሷን ለማስፋት ወደ ህንድ የተጏዘችው ኒሻ ጊሚሬ በደረሰባት የመኪና አደጋ ተጎድታ አልጋ ያዘች

በወራቶች ውስጥ ገንዘቧን ጨርሳ ቤተሰቦቿ ማሳከም አቃታቸው:: እነዚያ የተረባረቡባት ግለሰቦች እና ድርጅቶች ገሸሽ አሉባት! አብረሽን ስሪ ብለው የለመኗት ሁሉ ከእይታዋ ጠፉ

ጠያቂ የሌላት እና ሁለተኛ ላይ ያለውን አይነት ፎቶ እያነሱ ሶሻል ሚዲያ ላይ ለመለጠፍ ሊጎበኟት ከሚሄዱ ጥቂቶች በቀር ሰው አጣች::

በዚህ ሁሉ መሀከል ግን ዝነኛ በነበረችበት ወቅት አብራ እንድትስራ ጥያቄ አቅርቦላት ማናጀሯ "ይሄ ትንሽ ድርጅት ነው አይመጥንሽም" ብሎ ግብዣቸውን እንዳትቀበል ያደረገባት የስራ ፈጣሪዋ ሜግሃ ቻውድሃሪ የተባለች የድርጅቱ ባለቤት ህክምናዋን ሸፍና አሳከመቻት

በስተመጨረሻም የገዛ ማናጀሯ እንኳ ጥሏት ጠፋ

በወርሃ መስከረም 2021 ከረጅም ህመም እና ትግል በኃላ አረፈች:: ቤተሰቦቿ የቀብር ስርአቷን ለመፈፀም አቅም አልነበራቸውም ሆኖም ግን በዝናዋ ወቅት አብሬ አልሰራም ያለቻት ማግሃ ቻውድሃሪ ሙሉ ክፍያውን ከመሸፈኗም በላይ የቤተሰቦቿን የቤት ወጪም መሸፈኗን ቀጠለች

በዝናዋ ጊዜ አብረዋት የቆሙ ሁሉ በድካሟ ጊዜ ካጠገቧ ጠፉ!

አለምን ያስደመመው ቁንጅናዋ በሽታ ሲበላው ከጎኗ የሚቆም ጠፋ

ወዳጅ የተባሉት ሲሸሹ የራቀቻት ግን ከጎኗ ቆመች

አንዳንዴ በስኬታችን ጊዜ ያላሰብናቸው ሰዎች በውድቀታችን ጊዜ ያስቡናል!
ዛሬ ከጎንህ ማን አለ?! ??

(ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኘ)

* የ1.5 ሚሊየን ዜጎች የሚሊየነርነት እቅድ ብዙዎችን አነጋግሯል *በድጋሜ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ጨምሯል*ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ በአዲስ ነገር ብቅ ብለዋል። እነዚህን መረጃዎ...
18/10/2024

* የ1.5 ሚሊየን ዜጎች የሚሊየነርነት እቅድ ብዙዎችን አነጋግሯል
*በድጋሜ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ጨምሯል
*ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ በአዲስ ነገር ብቅ ብለዋል። እነዚህን መረጃዎች በዝርዝር በዩቲዩብ ቻናላችን ይመልከቱ። ሊንኩን በኮመንት መስጫው ከስር ያገኛሉ፡፡ ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ፡

16/08/2024

I love you ማለት እፈልጋለሁ አዳነች አቤቤን

ህዝቡን ይቅርታ ጠይቋል፡የአትሌቲክሱ አነጋጋሪ አሰልጣኝ በእራት ግብዣው ላይ ፕሬዚዳንቷ በተገኙበት ስለሽልማቱ በተናገረው ነገር ይቅርታ የጠየቀ ቢሆንም ይህንን ከጀርባ የሰሩትን ሰዎች ግን ይቅ...
14/08/2024

ህዝቡን ይቅርታ ጠይቋል፡

የአትሌቲክሱ አነጋጋሪ አሰልጣኝ በእራት ግብዣው ላይ ፕሬዚዳንቷ በተገኙበት ስለሽልማቱ በተናገረው ነገር ይቅርታ የጠየቀ ቢሆንም ይህንን ከጀርባ የሰሩትን ሰዎች ግን ይቅርታ እንደማይል ተናግሯል፡

ሁለት አውሮፕላኖች አየር ላይ ተጋጩ:: በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ አንድ የመለማመጃ አውሮፕላን ከመንገደኞች አውሮፕላን ጋር አየር ላይ ተጋጭቶ በደረሰ አደጋ የሁለት ሰው ሕይወት አለፈ። በሁለ...
05/03/2024

ሁለት አውሮፕላኖች አየር ላይ ተጋጩ::

በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ አንድ የመለማመጃ አውሮፕላን ከመንገደኞች አውሮፕላን ጋር አየር ላይ ተጋጭቶ በደረሰ አደጋ የሁለት ሰው ሕይወት አለፈ።

በሁለቱ አውሮፕላኖች ግጭት ሕይወታቸው ያለፈው በበረራ መለማመጃው አውሮፕልን ውስጥ የነበሩት የበረራ አስተማሪ እና ተማሪው መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

አውሮፕላኖቹ አየር ላይ ከተጋጩ በኋላ የበረራ መለማመጃ የሆነው አውሮፕላን በናይሮቢ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ብሔራዊ ፓርክ ወድቆ ውስጥ ወድቆ በመከስከሱ ነው ሁለቱ ሰዎች የሞቱት።

ከመለማመጃው አውሮፕላን ጋር የተጋጨው 44 ሰዎችን አሳፍሮ ተንደርድሮ ከተነሳ ንብረትነቱ ሳፋሪሊንክ ከተባለ አየር መንገድ አውሮፕላን ጋር ነው።

በግጭቱ ከባዱ አደጋ የደረሰው በመለማመጃው አውሮፕላን ላይ ሲሆን፣ መነገደኞችን አሳፍሮ የነበረው አውሮፕላን አደጋው ከተከሰተ በኋላ ተመልሶ ዊልሰን አየር ማረፊያ ለማረፍ ተገዷል።

በዚህም አደጋ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት 39 ተሳፋሪዎች እና 5 የበረራ ሠራተኞች ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰባቸው አየር መንገዱ ገልጿል። ወደ ኬንያዋ የባሕር ጠረፋ መዳረሻ ዲያኒ ሲያቀና የነበረው የመንገደኞች አውሮፕላን አየር ላይ ሳለ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ “ከተነሳ በኋላ ከባድ ድምፅ ያለው ነገር ተሰምቷል” ብሏል አየር መንገዱ ያወጣው መግለጫ።
African News

በአዲስ አበባ ከተማ በጆሮ ማዳመጫ እያዳመጡ መንገድ ማቋረጥ 80 ብር ያስቀጣል ተባለ የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር ...
05/03/2024

በአዲስ አበባ ከተማ በጆሮ ማዳመጫ እያዳመጡ መንገድ ማቋረጥ 80 ብር ያስቀጣል ተባለ

የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/ 2009 መሠረት በእግረኞች የሚፈፀሙ ጥፋቶች ላይ ቁጥጥር በማድረግ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ አስታውቋል ።ደንቡ ቀደም ባለው ጊዜ የወጣ ይሁን እንጂ በአፈፃፀሙ ዳተኝነት ሲታይበት ቆይቶ በአሁኑ ወቅት በእግረኞች የመንገድ አጠቃቀም ስህተት ሳቢያ የሚከሰት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ተብሏል ።

በዚህም መሠረት ደንቡን የሚተላለፉ እግረኞች ከ40 እስከ 80 ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚቀጡ በባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የዲጂታል ሚዲያ ከፍተኛ ባለሙያ አ/ቶ መኳንንት ምናሴ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

ከእግረኖች ደንብ መተላፎች መካከል ተገቢውን ጥንቃቄ ሳያደርጉ መንገድ ማቋረጥ ፣ ለተሽከርካሪ በተፈቀደ መንገድ ላይ ያለበቂ ምክንያት መቆም ፣ የእግረኛ መንገድ በሌለበት ቀኝ ጠርዝ ይዞ መጓዝ ፣ ለእግረኛ ተብሎ ከተከለለ መንገድ ውጭ መጓዝ እና በማንኛውም ሁኔታ ለእግረኞች እንቅስቃሴ እንቅፋት መሆን እያንዳንጃቸው በ40 ብር የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጡ ተጠቁሟል ።

በተጨማሪም ተለይተው የታጠሩ መንገዶችን ዘሎ ማቋረጥ ፣ በጆሮ ማዳመጫ እያዳመጡ መንገድ ማቋረጥ እንዲሁም እግረኞች እንዳያቋርጡ ክልክል በሆነ የማሳለጫ ወይም የቀለበት መንገድን ማቋረጥ እያንዳንዳቸው የ80 ብር ቅጣት እንደሚያስቀጡ አክለዋል ።

ሆኖም እግረኞች ይህን ተረድተው ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን ጥፋተኛ ሆኖ የገንዘብ ክፍያ መፈፀም ያልቻለ ሰው ፅዳትን ጨምሮ ተመጣጣኝ ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል ተብሏል ። የቁጥጥር ስራው በባለስልጣኑ 11 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ።
ዳጉ ጆርናል

የአፍሪካ ህብረት የአህያ ቆዳ ንግድን አገደ፡፡ህብረቱ በኢትዮጵያ ባካሄደው 37ኛዉ መደበኛዉ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ መጠናቀቁን ተከትሎ እሁድ ዕለት የሰጠዉን ዉሳኔ በዘርፉ የሚሰሩት በጎ አድ...
20/02/2024

የአፍሪካ ህብረት የአህያ ቆዳ ንግድን አገደ፡፡

ህብረቱ በኢትዮጵያ ባካሄደው 37ኛዉ መደበኛዉ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ መጠናቀቁን ተከትሎ እሁድ ዕለት የሰጠዉን ዉሳኔ በዘርፉ የሚሰሩት በጎ አድራጎት ድርጅቶች በደስታ መቀመበላቸዉን አስታዉቀዋል።

የእንስሳት በጎ አድራጊ ድርጅቶች አዉዳሚ እና አወዛጋቢ በማለት የጠሩትን "የአህያ ቆዳ ንግድ "
በአፍሪካ ህብረት በኩል መታገዱን ነዉ ካፒታል ለማወቅ የቻለዉ።

ብሩክ የተሰኘዉ በጎ አድራጎት ድርጅት ዉሳኔዉን ተከትሎ እንዳስታወቀዉ እገዳዉ በአህጉሪቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አህዮች ህጋዊ እርድ እንዲቆም ያደርጋል ብሏል።

በአፍሪካ ሁለት አስርት ዓመታት ለቻይና ባሕላዊ ሕክምና እና ለኮስሞቲክስ አገልግሎት ጥቅም ላይ የሚውለውን ጄልቲን ‘ኢጂአኦ’ ለማምረት የአህያ ቆዳ ተፈላጊ በመሆኑ ፍላጎቱም ከቻይና የተነሳ መሆኑ ይነገራል።

በአፍሪካ በአጠቃላይ 53 ሚሊዮን ያህል አህዮች እንዳታላት የሚገመት ሲሆን ወደ 8 ሚሊዮን ገደማ የሚሆነዉን ድረሻ የሚይዘዉ በሀገራቶች ተፈላጊ የሆነዉ አህያ ደግሞ በኢትዮጵያ ይገኛል ተብሎ ይታመናል ።

Capital

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጉድ አዲስ - Good Addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share