23/10/2022
ፔሌ ከብሔራዊ ቡድኑ ብራዚል ጋር የዓለም ዋንጫን ሶስት (3) ጊዜ በማንሳት በዓለም ላይ እስካሁን ብቸኛው ተጫዋች ነው፡፡ (በ1958 ስዊድን፣ በ1962 ቺሊ እና በ1970 ሜክሲኮ)፡፡ ከእርሱ በመቀጠል በ2ኛነት 20 ተጫዋቾች ሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ከብሔራዊ ቡድናቸው ጋር አንስተዋል፡፡
የምንግዜም ታላቅ ተጫዋች የሚባለው ብራዚላዊ አድሰን አራንትስ ዶ ናሲሚቶ (ፔሌ) በፊፋ "ታላላቅ" ከሚባሉት ተጫዋቾች መሀል አንዱ ሆኖ ተቀምጧል፤ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ከስኬታማና ታዋቂ ተጫዋቾች መሀል ነው፡፡ በ1999 በአለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የ20ኛው ክፍለ ዘመን አትሌት እንዲሁም ታይም መፅሔት የ20ኛው "ክፍለ ዘመን" 100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ውስጥ ፔሌን አካቶታል፡፡
በተጨማሪም በ2000 በፊፋ የክፍለ ዘመኑ ኮከብ ተጫዋች ሽልማት ፔሌና ማራዶና በጣምራ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ (የዓመቱ ሳይሆን "የክፍለ ዘመኑ ኮከብ")፡፡
ፔሌ የወዳጅነትን ጨምሮ ጠቅላላ በተጫወተበት 1,363 ጨዋታ 1,279 ግብ በማስቆጠር የጊነስ ዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ስሙን አስፍሯል፡፡
ከ1995-98 የብራዚል ስፖርት ሚኒስቴር ሆኖም ሀገሩን አገልግሏል፡፡
HBD ፔሌ 82ኛ ዓመት ዛሬ የተወለደበት ቀን ነው፡፡