ሸገር አዲስ/sheger addis

ሸገር አዲስ/sheger addis አዲስ መረጃ የሚከታተሉበት ገፅ
ስፖርት
መዝናኛ
ወቅታዊ
አዳዲስ መረጃ
(1)

የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ምልከታ ይፋ አደረገ [ሸገር አዲስ ሚዲያ ግንቦት 28/2018]​የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ወቅት ያከ...
05/06/2026

የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ምልከታ ይፋ አደረገ

[ሸገር አዲስ ሚዲያ ግንቦት 28/2018]

​የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ወቅት ያከናወነውን አገር አቀፍ የታዛቢነት የክትትል ሥራ ሪፖርት እና የሚዲያ መግለጫ በአዲስ አበባ ሰጥቷል።

​ፌደሬሽኑ በመላ አገሪቱ ከ14 ሺህ በላይ ታዛቢዎችን በመመደብ፣ ከ25 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን መሸፈን መቻሉን አስታውቋል።

ከተመዘገቡት አጠቃላይ መራጮች ውስጥ የሴቶች ቁጥር 49.3 በመቶ መድረሱ እና የባዮሜትሪክ የቴክኖሎጂ ምዝገባ ለመጀመሪያ ጊዜ መተግበሩ በምርጫው የታዩ ዋና ዋና ጥንካሬዎች መሆናቸውን ፌደሬሽኑ ገልጿል።

​በሌላ በኩል በጋምቤላ ክልል የምርጫ ጣቢያዎች በሰዓቱ አለመክፈትና በአንዳንድ አካባቢዎች በሴት መራጮች ላይ የተስተዋሉ ጫናዎች፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሙ የጸጥታ ስጋቶች እንዲሁም በአዲስ አበባ የታየው የዲጂታል ምዝገባ ሥርዓት አለመቀናጀት በሂደቱ ላይ የታዩ ተግዳሮቶች መሆናቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል።

​ፌደሬሽኑ ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የደህንነት ስጋቶችን ለመከላከል የጸጥታ አካላትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል። በቀጣይም የምርጫ አስፈጻሚዎች በቂ ስልጠና እንዲያገኙ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢያንስ 30 በመቶ የእጩዎች ቁጥር ለሴቶች እንዲያደርጉ ምክረ-ሃሳቡን አቅርቧል።

ጠቃሚ የሞባይል አገልግሎት ኮዶች​* #06 # — የስልኩን ኢንተርናሽናል  #መለያ ቁጥር ማወቂያ (IMEI)​* #9998*246 # — የስልኩን ባትሪ እና ሜሞሪ መረጃዎች ማወቂያ​*21*900 ...
05/06/2026

ጠቃሚ የሞባይል አገልግሎት ኮዶች

​* #06 # — የስልኩን ኢንተርናሽናል #መለያ ቁጥር ማወቂያ (IMEI)

​* #9998*246 # — የስልኩን ባትሪ እና ሜሞሪ መረጃዎች ማወቂያ

​*21*900 # — ስልክህ እንዳይደወልበት ለማድረግ

​*67*የፈለጉት ቁጥር # — ስልክ ዳይቨርት (Divert) ለማድረግ

​ #67 # — ዳይቨርቱን ለማጥፋት

​*43 # — Call waiting Active ለማድረግ

​ #31 #09..... # — ስትደውል ቁጥርህ እንዳይታይ ለማድረግ

​*21*857 # — ሲደወልልህ እንዳይሰራ ለማድረግ

​ #002 # — እንዳይሰራ ያደረግከውን ለማቋረጥ

"ሰኔ እና ሰኞ... አይግጠም"..🤔ሰኔ እና ሰኞ አይግጠም የሚለው የቆየ የአባቶቻችን አባባል  ዘንድሮም በ 2018 ዓ.ም. በአይናችን ልናየው በትክክል ገጥሟል። ሰኔ 1 ቀን ሰኞ ይውላሎል።ከ...
04/06/2026

"ሰኔ እና ሰኞ... አይግጠም"..🤔

ሰኔ እና ሰኞ አይግጠም የሚለው የቆየ የአባቶቻችን አባባል ዘንድሮም በ 2018 ዓ.ም. በአይናችን ልናየው በትክክል ገጥሟል። ሰኔ 1 ቀን ሰኞ ይውላሎል።
ከ 1979 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ዛሬ... በከፊል እንይ እስኪ..

1)1979 ዓ.ም. ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም አገሪቱ በከባድ ፈተና ውስጥ ነበረች የ1977ቱ ታላቁ ድርቅ መዘዝ እና በወቅቱ የነበረው የዝናብ እጥረት ተከስቶ ነበረ።

2) 1984 ዓ.ም. በዚህ ወቅት ሰኔ እና ሰኞ በድጋሜ ገጠሙ። ህይ ዓመት የሽግግር ወቅት ቀውስ እንደነበረ የታሪክ መዛግብቶች በጥልቀት ያወሱናል። በዚህም ወቅት በመላው አገሪቱ ከፍተኛ የጸጥታ መደፍረስ ና ግጭት ነገሰ።

3) 1990 ዓ.ም. በዚህም ወቅት ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም በአገሪቱ ላይ ሊላ የደም ምዕራፍ ተከፈተ።በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የተነሳው እጅግ አስከፊ የነበረው የባድሜ የድንበር ጦርነት በዚሁ አመት ፈነዳ።

4) 1997 ዓ.ም. በ 1997 ላይ ደግሞ ታሪኩ ይበልጥ ልብ ሰባሪ ሆኗል።1997 ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ። ያ ታዋቂው እና ውጥረት የበዛበት አገራዊ ምርጫ 97 የተካሄደው በዚህ ወቅት ነበር።

5) በ2007 ዓ.ም. ከ 10 ዓመታት በኋላ በ 2007 ዓ.ም. በድጋሜ ሰኔ እና ሰኞ ገጠሙ።

6) 2013 ዓ.ም. በቅርብ ጊዜ ትውስታችን በሆነው በ 2013 ዓ.ም. ሰኔ እና ሰኞ በድጋሜ ገጠሙ። በዚህም ወቀት የጦርነት የጭንቀት የከበሮ ድምፅ የነበረ መሆኑን ሁላችንም እናስታውሳለን።

የታሪክ ፍሰት አያችሁ? አሁን ደግሞ ወደ ዘንድሮ እንምጣ። ዘንድሮ 2018 ዓ.ም. ነው።አመቱም ድጋሜ ሰኔ እና ሰኞ ገጥመዋል። እንደ 1997ቱ, እና 2007ቱ ሁሉ:ዘንድሮም መውደቃቸው ታዘባቸሁ? ታሪክ እራሱን ይደግማል? ወይንስ እኛ ካለፈው ተምረን ራሳችንን እና አገራችንን እንጠብቃለን? የዘንድሮው የሰኔ እና ሰኞ ገጠመኝ ለኢትዮጵያ ወጣቶች የጥንቃቄ የማስተዋል እና የሰላም ጊዜ ይሁንልን።

አባቶቻችን በምክንያት ነው ሰኔ እና ሰኞ ያሉት ሰላም ለኢትዮጵያ 🇪🇹

የኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ መግለጫ[ሸገር አዲስ _ ሚዲያ 26/2018 ዓ.ም] የኢጋድ (IGAD) እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች በኢትዮጵያ በተካሄደው 7ኛው አጠ...
03/06/2026

የኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ መግለጫ

[ሸገር አዲስ _ ሚዲያ 26/2018 ዓ.ም]

የኢጋድ (IGAD) እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች በኢትዮጵያ በተካሄደው 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ዙሪያ የጋራ መግለጫ ሰጡ።

በኢትዮጵያ ግንቦት 24/ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ላይ የተሰማሩት የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ (IGAD) ታዛቢዎች የመጀመሪያ ደረጃ ሂደቱን ይፋ ማድረጋቸውን የኢጋድ ቃል አቀባይ ፔሸንስ ንያንግ አስታውቀዋል።

​ታዛቢዎቹ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ሶማሌ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ክልሎችና ከተሞች ተሰማርተው የምርጫውን ሂደት በቅርበት ሲከታተሉ ሰንብተዋል።

በዚህ የጋራ መግለጫ መድረክ ላይ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ እንዲሁም የኢጋድ ታዛቢ ቡድን መሪ እና የቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌን ጨምሮ በርካታ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ጋዜጠኞች ተገኝተዋል።

በዝርዝር እምንመለስበት ይሆናል

የአርሰናል ደጋፊዎች የድል በዓል ዝግጅት[ሸገር አዲስ _ሚዲያ ) 25/2018]የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚካሄደው ታላቅ የአርሰናል ደጋፊዎች የድል በዓል ዝግጅት ጋዜጣዊ መግለጫ...
02/06/2026

የአርሰናል ደጋፊዎች የድል በዓል ዝግጅት

[ሸገር አዲስ _ሚዲያ ) 25/2018]

የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚካሄደው ታላቅ የአርሰናል ደጋፊዎች የድል በዓል ዝግጅት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ።

​የእንግሊዙ አርሰናል ክለብ ከ22 ዓመታት በኋላ የተቀዳጀውን ታላቅ ድል ለመዘከር ቫርዳስ ኢንተርቴይመንት ከአዋሽ ባንክ እና ከሐበሻ ቢራ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ይህ ታሪካዊ ክስተት፤ የኢትዮጵያን ደጋፊዎች ፍቅርና አንድነት ለዓለም የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።

​በዝግጅቱ ላይ ከ10 በላይ ታዋቂ ድምጻውያን እና ዲጄዎች ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ታዋቂው የዓለም አቀፍ ደጋፊዎች ሚዲያ ኤ ኤፍ ቲቪ (AFTV) በቦታው ይገኛል።

ከሁሉም በላይ ደግሞ የቀድሞው የአርሰናል ኮከብ ተጫዋች አማኑኤል ኢቦዌ (Emmanuel Eboué) ቅዳሜ ረፋድ 7 ሰዓት ላይ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግለት ተበስሯል።

​ታዳሚዎች በዕለቱ ከረጅም ሰልፍ እንዲድኑ ትኬቶች በአዋሽ ባንክ ቅርንጫፎች፣ በወኪሎች እና በአዋሽ ብር ፕሮ የሞባይል መተግበሪያ እየተሸጡ ይገኛል። ቀድመው ለገዙና በስታዲየም ለሚገዙ ሰዎችም ነፃ ልዩ ቲሸርቶች ተዘጋጅተዋል።
​የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚካሄደው የዚህ ታላቅ ዝግጅት የበር መክፈቻ ሰዓት ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸው፣ ደጋፊዎች በሰዓቱ እንዲገኙ ጥሪ አቅርበዋል።

አንቶኔላ የሜሲ ሚስት"እውነቱን ለመናገር መጀመሪያ ላይ ቀስ በቀስ ታዋቂ እና ሀብታም እየሆነ ሲመጣ ሜሲን አጣዋለው ብዬ በጣም መፍራት ጀምሬ ነበር።""በዚህ የተነሳ ለተወሰነ ጊዜ በጣም ተጨን...
02/06/2026

አንቶኔላ የሜሲ ሚስት

"እውነቱን ለመናገር መጀመሪያ ላይ ቀስ በቀስ ታዋቂ እና ሀብታም እየሆነ ሲመጣ ሜሲን አጣዋለው ብዬ በጣም መፍራት ጀምሬ ነበር።"

"በዚህ የተነሳ ለተወሰነ ጊዜ በጣም ተጨንቄ ነበር በቃ ከአሁን አሁን ጥሎኝ ሄደ እያልኩ እሰጋ ነበር ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ወደ ዝና ከፍ ሲሉ በዙሪያቸው የነበሩ ሰዎችን ይረሳሉ።"

"ታውቃላችሁ ከልጅነታችን ጀምሮ አብረን ነው ያደግነው እና ፍቅሬን እንዴት እንደምገልፅለት አላቅም ነበር ግን በቃ ሆነ ሁለታችንም በፍቅር ዓለም ውስጥ መሆናችንን ተግባባን።

እሱም በቀሪው ሕይወቴ ከጎኔ እንደሚሆን ሲነግረኝ በጣም ደስ አለኝ ቃል የገባውን ነገር እንደሚፈፅም እና ታዓማኝ እና ፍቅር አሰጣጡን በሀገሩ አርጀንቲና እና በባርሴሎና ስላየሁት እንደዚያ ካለኝ ቀን በኋላ ምንም ፍርሃት አጋጥሞኝ እንኳ አያውቅም እሱን አጣለሁ የሚል ይሃው ተመስገን እሰከአሁንም አብረን አለን።"

Football Era

ሀሊማ ባል ማግባት አትፈልግምሰይፉ ሾ ላይ ቀርባ አግቢ አታግቢ ክርክሩ ረጅም ሰዓት ፈጀ ሆኖም ሀሊማ አልተሸነፈችም ባል አግብታ የት ወጣሽ የት ገባሽ የሚላት ሰው እንዲኖር አትፈልግም፣ ሰይፉ...
01/06/2026

ሀሊማ ባል ማግባት አትፈልግም

ሰይፉ ሾ ላይ ቀርባ አግቢ አታግቢ ክርክሩ ረጅም ሰዓት ፈጀ ሆኖም ሀሊማ አልተሸነፈችም ባል አግብታ የት ወጣሽ የት ገባሽ የሚላት ሰው እንዲኖር አትፈልግም፣ ሰይፉ እዚህ መሀል ጠየቀ

"ከአለማየሁ ደመቀ ጋር 20 አመት ኖራችሁ የለም ወይ አላት"
"በወንድምነት ነው" አለች

ከወንድ ጋር አንድ ቤት መኖር ስለማትፈልግ፣ ለመውለድ እድሜዬዋ ስለሄደ፣ 11 ጊዜ ሚዜ የሆነችባቸው ትዳሮች መፍረሳቸው፣ ምናልባት "አላህ ከፈቀደ አገባለሁ"አለች በመጨረሻ።

እና ለትውልዱ ምን ያስተምራል መውለድ ማግባት ወግ ማዕረግ የሚባለውን እሴት አለመውለድ ትዳር አልባ ሆኖ መኖርን ልክ እንደ መልካም ነገር በሚድያ ቀርቦ ማውራት ምን ይባላል።

ሚስት ባሏን ደሀ ነህ ብላ በፈታች በማግስቱ ባል 273 ሚሊዮን ዶላር ሎተሪ አሸነፈ።ሰውዬው ለተወሰነ ጊዜ ሥራ አጥ ነበር እና ሚስቱ በሂደቱ ላይ እምነት መጣል ትዕግስት ስለሌላት ወደ ፊት ለ...
31/05/2026

ሚስት ባሏን ደሀ ነህ ብላ በፈታች በማግስቱ ባል 273 ሚሊዮን ዶላር ሎተሪ አሸነፈ።

ሰውዬው ለተወሰነ ጊዜ ሥራ አጥ ነበር እና ሚስቱ በሂደቱ ላይ እምነት መጣል ትዕግስት ስለሌላት ወደ ፊት ለመቀጠል ወሰነች። ሆኖም የፍቺ ሰነዶችን ከፈረመ ከአንድ ቀን በኋላ ህይወቱን ሙሉ በሙሉ የሚለዉጠውን ሎተሪ አሸንፏል።🫣

አንቸኩል ለማለት ነው ጎበዝ

መልእክቴ ስራ የለህም ገንዘብ የለህም እያንዳንዱ ቀን እድል ይዞ ይመጣል ወዳጄ ዛሬ ስታልፈው ነገ ፈጣሪ ላንተ ምን እንዳዘጋጀ አታውቅም ሰዎችንም በማጣት እና በማግኘት አይሁን ቀረቤታህ።

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ለመቄዶንያ ባበረከቱት ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ከፍተኛ ምስጋናና ክብር ተቸራቸው! #ሸገር አዲስ -ሚዲያ​[ «ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!» የሚለውን ታላቅ መርህ በተ...
31/05/2026

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ለመቄዶንያ ባበረከቱት ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ከፍተኛ ምስጋናና ክብር ተቸራቸው!
#ሸገር አዲስ -ሚዲያ
​[ «ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!» የሚለውን ታላቅ መርህ በተግባር ያሳዩት የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፤ ለአረጋውያንና የአእምሮ ህመምተኞች መርጃ ማህበር (መቄዶንያ) ካበረከቱት ታላቅ ስጦታ ጋር ተያይዞ በዛሬው ዕለት ደማቅ የምስጋና እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተከናወነ።

​ብፁዕነታቸው ቀደም ሲል ለድርጅቱ ያበረከቱት ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ መኖሪያ ቤት የመቄዶንያ 57ኛ ቅርንጫፍ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ ይህንን ውድ መስዋዕትነት ለመዘከር የመቄዶንያ አረጋውያን፣ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዋናው ግቢ ልዩ የክብር ፕሮግራም ተሰናድቶላቸዋል።

​❖ የክብር ሰርተፊኬት አሰጣጥ እና የክብር እንግዶች

​በዕለቱ የሲዳማ እና ጌዲዮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ በመገኘት፣ ለመቄዶንያ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የተጣለባቸውን ኃላፊነት በታማኝነት እንደሚወጡ በመግለጽ የላቀ የምስጋና ሰርተፊኬት ለብፁዕ አቡነ ፋኑኤል አበርክተዋል።

​በዚህ ታሪካዊና መንፈሳዊ ፕሮግራም ላይ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦችና የሃይማኖት አባቶች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል፦

​የመቄዶንያ አምባሳደር ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ እና ሌሎች ዘማርያን

​ኡስታዝ ጀማል (የአብሮነትና የመረዳዳት ተምሳሌት በመሆን)

​ዶክተር ጌትነት ፈለቀ

​በርካታ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ አካላት እና የክብር እንግዶች በድምቀት ታድመዋል።

​❖ "ተሸክሜው መቃብር አልወርድም!" — ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል

​ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በዕለቱ ባደረጉት ልብ የሚነካ ንግግር፣ ስጦታውን እንዲያበረክቱ ያነሳሳቸውን አምላክ እያመሰገኑ የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ እንዲህ ሲሉ ገልጸዋል፦

​"ይህንን ንብረት ተሸክሜው መቃብር አልወርድም። ይህንን ታላቅ ስጦታ እንዳበረክት ያነሳሳኝና ያጠነከረኝ ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!"
​አክለውም መቄዶንያን መርዳት ሃይማኖታዊና ዜግነታዊ ግዴታ መሆኑን በማሳሰብ፤ "ለተቸገሩት የሰጠ ለእግዚአብሔር ያበድራል፤ በሰማይም የሚመዘንልን የሰራነው በጎ ስራ ነውና ሁላችንም በቻልነው አቅም የተራቡትን እናብላ፣ የተጠሙትን እናጠጣ፣ የታረዙትን እናልብስ" በማለት ለህዝበ ክርስቲያኑና ለበጎ አድራጊዎች በሙሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

​የመቄዶንያ አረጋውያንም በብፁዕነታቸው መልካም ተግባር መጽናናትንና ትልቅ ተስፋን ማግኘታቸውን በመግለጽ ፈጣሪ እድሜና ጤና እንዲሰጣቸው በጋራ መርቀዋል።

ቀድሞ ደራሽ፥ እንባ አባሽ‼️ ለደስታና ለጭፈራ የቡድን ጓደኞቹ ጋር አልሄደም፤ ፈንጠዚያን አላስቀደመም፤ ይልቁንስ ቀን ጎድሎበት በድንጋጤ ደርቆ ወደ ቆመው፥ በብርሃን መሃል በጨለማ ወደተዋጠው...
31/05/2026

ቀድሞ ደራሽ፥ እንባ አባሽ‼️

ለደስታና ለጭፈራ የቡድን ጓደኞቹ ጋር አልሄደም፤ ፈንጠዚያን አላስቀደመም፤ ይልቁንስ ቀን ጎድሎበት በድንጋጤ ደርቆ ወደ ቆመው፥ በብርሃን መሃል በጨለማ ወደተዋጠው፥ ወደ ብሄራዊ ቡድን ተጣማሪው፥ ወደ ሀገሩ ልጅ ፈጥኖ ገሰገሰ፤ ከሁሉ ቀድሞ ደረሰና ለረጅም ደቂቃ አቅፎት አፅናናው፤ እንባውን አበሰለት፤ አይዞህ ወንድሜ አለው

የ32 አመቱ ብራዚላዊ የፒኤስጂ አምበል ማርከስ አኦስ ኮሪአ፥ ማርኪኒዮስ፥ ትናንት በሻምፒዮንስ ሊጉ ፍፃሜ በአለም ፊት ያሳየው ሰዋዊ እዝነት የሚሊዮኖችን ልብ ነክቷል

ከማርኪኒዮስ በአራት አመት የሚያንሰው የ28 አመቱ ገብርኤል ዶ ሳንቶስ ማጋሊሽ ክለቡ አርሴናል እዚህ ደረጃ እንዲደርስ የእሱ ሚና ከፍተኛ ነበር፤ የቡድኑ ምሰሶ ሆኖ ሰንብቷል፤ ትናንት በጨዋታውም ሜዳ ላይ ከነበሩት የሁለቱ ቡድኖች ተጫዋቾች መካከል ብዙ ኳስ ያመከነው እሱ ነው፤ 13 ኳሶችን ተከላክሎ አውጥቷል፤ መጨረሻው ግን አላማረም፤ ቀን ጣለው፥ እድልና ድል ፊቱን አዞሩበት፤ እንደ ሮቤርቶ ባጂዮና ጆን ቴሪ፥ እንደ ዴቪድ ትሪዚጌና ቡካዮ ሳካ በታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ ወሳኝ መለያ ምት ስቶ በህይወቱ ጥላ ሆኖ የሚከተለው አስቀያሚ ታሪክ አጋጠመው

በዚያች ቅፅበት አሸናፊዎቹ ፒኤስጂዎች ሜዳው አልበቃ ብሏቸው በደስታ ማዕበል ሲናጡ ከእነሱ ወገን የሆነው ማርኪኒዮስ ግን ተነጥሎ ወደ አርሴናሉ ተከላካይ ሄደ፤ እጁን አፉ ላይ ጭኖ በደመነፍስ የሚራመደው ገብርኤል ጋር ሲደርስ ማርኪኒዮስን ማንም አልቀደመውም፤ በስታዲየሙ ከሚሰማው የደስታ ጩኸት በላይ ጎልቶ በወጣ ልባዊ ፍቅር ምድር የዞረችበትን የሀገሩን ልጅ አፅናናው፤ እንደ ወንድሙ፥ እንደ ልጁ አጥብቆ ይዞ አበረታው፤ ልብ የሚነካ ነበር፤ የአርሴናሉ አምበል ማርቲን ኦዲጋርድም ለማርኪኒዮስ ተግባር ያለውን ክብርና አድናቆት ከምስጋና ጋር አቅርቧል

ሁለቱ ብራዚላዊያን፥ ሁለቱ ሳኦፖሎ ተወልደው ያደጉ ተጫዋቾች፥ ሁለቱ የመሀል ተከላካዮች ማርኪኒዮስና ገብርኤል እስካሁን በብሄራዊ ቡድን 16 ጨዋታዎችን በጋራ ተጣምረው ተጫውተዋል፤ በቀጣዩ የአለም ዋንጫም የተከላካይ ክፍሉን ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል

የአራት ልጆች አባቱ ማርኪኒዮስ በርካታ ክብረወሰኖችን በስሙ አስመዝግቧል፤ በሁለት ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜዎች በአምበልነት ዋንጫ ያነሳ የመጀመሪያው ብራዚላዊ ሆኗል፤ በአውሮፓ መድረክ 122 ጨዋታዎችን የተጫወተ ቀዳሚው ብራዚላዊ ለመባልም በቅቷል፤ በ13 አመታት የፒኤስጂ ቆይታው ለክለቡ ብዙ ጨዋታ ያደረገ፣ 11 የሊጉን ዋንጫ ጨምሮ በጥቅሉ ከ40 በላይ ዋንጫዎችን ያመጣና ሌሎች ስኬቶችን ያገኘ አምስት ቁጥር ለባሽ ደጀን ለመሆን በቅቷል

ትናንት ደግሞ በአምበልነቱ ዋንጫውን በአለም ፊት ከሁሉ ቀድሞ በከፍታ ከማንሳቱ በፊት ልዩ ሰብአዊ ምግባር ፈፅሞ በአለም ፊት ስሙን በክብር ከፍ አድርጓል፤ ማርኪኒዮስን መሳይ የሃገር ልጅ፥ እሱን መሳይ አርአያ ሰብ፥ ከደስታ መሀል ያዘነውን የሚፈልግ ፈጥኖ ደራሽና እንባ አባሽ በምድሪቷ ላይ ይብዛ!

(ታምሩ ዓለሙ)

Address

Ferensaye Legasion
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸገር አዲስ/sheger addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share