Sheka TV

Sheka TV This is the official Sheka TV page - where you can get all the latest news in Amharic, Sheki Noono, Majang.

ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው፡- የህንዱ ሚዲያ 'ፈርስት ፖስት' ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ተቋም የሆነው 'ፈርስት...
07/08/2026

ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው፡- የህንዱ ሚዲያ 'ፈርስት ፖስት'

ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ተቋም የሆነው 'ፈርስት ፖስት' በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ ባሰራጨው ወደ ዘጠኝ ደቂቃ በሚጠጋ ጥልቅ ትንታኔው ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር እያደረገች መሆኗን ዘግቧል።

ሚዲያው በዘገባው እንዳስገነዘበው፣ ለረጅም ዓመታት በጦርነትና በድርቅ ትታወቅ የነበረችው ኢትዮጵያ፣ ዛሬ ላይ ይህንን የተዛባ ትርክት በመቀየር በኢነርጂ፣ በአቪዬሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ መስኮች የአፍሪካ ኃያል ሀገር ለመሆን በተግባር እየሰራች ትገኛለች።

እንደ 'ፈርስት ፖስት' ዘገባ ከሆነ፣ ለዚህ ታላቅ ሀገራዊ ሽግግር ዋነኛ ሞተር የሆነው ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው።

ይህ ግድብ ከየትኛውም የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ብድር ሳይወሰድበት በኢትዮጵያውያን የገንዘብ፣ የላብና የደም አስተዋጽኦ ብቻ መገንባቱ፣ አፍሪካውያን የራሳቸውን ህልም ማሳካት እንደሚችሉ ያረጋገጠ ትልቅ ራስን የመቻል ማሳያ መሆኑን ሚዲያው አብራርቷል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ የቀጣናው የትስስር ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ተቋሙ አድንቋል።

በአቪዬሽኑ ዘርፍም ቢሆን በ12.5 ቢሊዮን ዶላር እየተገነባ ያለው አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ይህም አዲስ አበባን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፣ የንግድና የቱሪዝም ዋነኛ መገናኛ እንደሚያደርጋት 'ፈርስት ፖስት' አትቷል።

ከዚህ ጎን ለጎንም የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገ ያለው የማዕድን ዘርፍ እና በሶማሌ ክልል እየተገነባ ያለው ግዙፉ የማዳበሪያ ፋብሪካ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ዘገባው አካቷል።

'ፈርስት ፖስት' በዘገባው እንደጠቀሰው፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በኢንቨስትመንት ማሻሻያዎች ረገድ ኢትዮጵያ አስደማሚ ለውጦችን እያሳየች ነው።

የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስኬት፣ የቴሌኮም እና የባንክ ዘርፎች ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት መሆን፣ እንዲሁም የካፒታል ገበያ መጀመር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በእጅጉ እንደሚያሳድገው ተጠቅሷል።

የብሪክስ አባል የሆነችው ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም ጋር በመተባበር እያካሄደች ያለው ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ በቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ መሆኑን የህንዱ ሚዲያ 'ፈርስት ፖስት' ለዓለም ዘግቧል።

በከተማው የገበያ መረጋጋትን ይፈጥራል የተባለው የቴፒ ከተማ የግብይት ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ ነው፤የማዕከሉ ስራ መጀመር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የከተማው ንግድ ጽህፈት ቤት አስታውቋል...
07/08/2026

በከተማው የገበያ መረጋጋትን ይፈጥራል የተባለው የቴፒ ከተማ የግብይት ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ ነው፤

የማዕከሉ ስራ መጀመር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የከተማው ንግድ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

በማዕከሉ ውስጥ ሲገበያዩ ያነጋገርናቸው ሸማቾች የተለያዩ ምርቶች በማዕከሉ እየቀረቡ መሆኑን ተከትሎ ዋጋው ተመጣጣኝና ከመደበኛ ገበያ ከምሸጡት የተሻለ መሆኑን ገልፀዋል።

የሰላም ሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበር የሸቀጣ ሸገጥ መሸጫ ሱቅ አስተባባሪ መ/ር ከማል አዩብ እንደገለፁት አከባቢው እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ንረት ለመቅረፍ ማዕከሉ መቋቋሙ ለህብረተሰቡ እፎይታን የሚሰጥ በመሆኑ በማዕከሉም የዋጋ ቅናሽ በሁሉም ምርቶች በመኖሩ ህብረተሰቡ በስፍራው በመምጣት ልገበያይ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በከተማ አስተዳደር ድጋፍ በአጠቃላይ ሀያ ዘጠኝ ሸዶችን ይዞ ስራ መጀመሩን የተናገሩት የቴፒ ከተማ አስተዳደር ኢንዱሲትርና ንግድ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አብነት አድራሮ ይህም የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም በዚህም ለበርካቶ የስራ ዕድል መፍጠር የተቻለ መሆኑን እንዲሁም ህብረተሰቡ በአንድ ማዕከል የፈለገውን ምርት ማግኘት የሚችልበት ና በቅናሽ ዋጋ መገበያየት የሚችልበት ህደት ተፈጥሯል ብለዋል።

በአጠቃላይ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የኑሮ ውድነት ለመቀነስ ታቅዶ የተሰራ በመሆኑ ህብረተሰቡ ልበያይ እንደሚገባ እንዲሁም ለሎች ማዕከላት እንደሚስፋፉም ተገልሏል።

ዘጋቢ:ምንታምር አስፋው

07/08/2026

የሐይማኖት አባቶች ፀሎትና ቡራኬ እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ምረቃት- ለስኬታማ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ውሎ

ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም

የአጀንዳ የሥራ ቡድኖች የምክክር ሒደቱን በይፋ ጀመሩ በስልታዊ ቡድኖች ተደራጀተው የቀረቡ የምክክር ምክረ ሃሳቦች 500 አባላት ላሉት ለአጀንዳ የሥራ ቡድን ቀርበዋል አለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ...
06/08/2026

የአጀንዳ የሥራ ቡድኖች የምክክር ሒደቱን በይፋ ጀመሩ

በስልታዊ ቡድኖች ተደራጀተው የቀረቡ የምክክር ምክረ ሃሳቦች 500 አባላት ላሉት ለአጀንዳ የሥራ ቡድን ቀርበዋል አለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፡፡

መድረኩ በእያንዳንዱ የአጀንዳ የሥራ ቡድን ሁለት የተደራጁ የቃለ ጉባዔ ሃሳቦች የተነበቡ ሲሆን÷ የሁለቱ ቡድኖች ሃሳቦች በአጀንዳ ተቀራራቢነት፣ ተመጋጋቢነት እና ልዩነት በተመካካሪዎች እንዲታይ እድል ሰጥቷል፡፡

ተመካካሪዎች ከሁለቱ ስልታዊ ቡድኖች ሃሳቦችን እንዲያቀናጁ 30 አባላት ያሉበትን የምክረ ሃሳብ አቀናጆችን መምርጣቸው ተመላክቷል፡፡

በቀጣዮቹ ቀናት የስልታዊ ቡድኖች ሃሳቦች በተመረጡ አቀናጆች ተዋህደው እንደሚቀርቡም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

የልማትና የቱሪዝም አዲስ ብሥራት በባሕር ዳር ከቦሌ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ተመረቀጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ...
06/08/2026

የልማትና የቱሪዝም አዲስ ብሥራት በባሕር ዳር ከቦሌ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ተመረቀ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ በኢትዮጵያ ሁለተኛው ግዙፍ የሆነውን የባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል መርቀው በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ባሕር ዳር የኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም እና የዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ማዕከልነቷ ይበልጥ እየጎላ መምጣቱን ገልጸዋል።

አዲሱ ተርሚናል በከተማዋ ለተከናወኑት እና እየተከናወኑ ላሉት ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ትልቅ የኢኮኖሚ እና የንግድ እንቅስቃሴ ብሥራት እንደሚሆን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከተማዋ ከቱሪዝም አቅሟ በተጨማሪ በኢንዱስትሪው መስክ ያላትን ከፍተኛ አቅም ለመጠቀም የኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነባባት፣ በምሳሌነት የሚጠቀሱ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ባለቤት እንዲሁም በግዝፈቱ እና በጥራቱ ተወዳዳሪ የሌለው ታላቅ ድልድይ የተገነባባት ከተማ መሆኗን አብራርተዋል።

በከፍተኛ ጥራት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት ይበልጥ በማሳደግ የሀብት እና የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከል የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ ለቱሪዝም ያላትን ተመራጭነት ያጎላዋል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።

በከተማዋ እየተገነባ የሚገኘው ስታዲየም ሲጠናቀቅ ከሀገር ውስጥ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚመጡ በርካታ እንግዶችን አስተናጋጅ በመሆን የከተማዋን ውበት፣ ታሪክ እና መልካም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅ እንደሚሆን አብራርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አዲሱ ተርሚናልን መረቁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከቦሌ ...
06/08/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አዲሱ ተርሚናልን መረቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ሁለተኛውን ግዙፍ የሆነውን የባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አዲሱ ተርሚናልን በባሕር ዳር ከተማ መርቀው ከፍተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ባሕር ዳር ከተፈጥሮ ፀጋዋ በተጨማሪ የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ የልማት እንዲሁም የብልጽግና ምሳሌ መሆን የምትችል ታሪክ ጠገብ ከተማ መሆኗን ገልጸዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቱሪዝም፣ በኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ፣ በውስጥ ለውስጥ መንገዶች፣ በግዙፉ የዓባይ ድልድይ እና በኮሪደር ልማት ከተማዋ ከፍተኛ መነቃቃት ውስጥ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

የዛሬው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም ቀድሞ የነበረው አሮጌ ተርሚናል በግጭት ምክንያት መመታቱን ተከትሎ ችግሩን ወደ መልካም እድል በመቀየር ለትውልድ የሚሻገር የተሻለና ያማረ ፕሮጀክት ዕውን ማድረግ መቻሉን አውስተዋል።

አያይዘውም የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍትህን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የጀመረውን የቨርቹዋል ችሎት አሠራር በአብነት አንስተው አድንቀዋል።

ከዚህ ግዙፍ የልማት ሥራ ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለክልሉ ሕዝብና አመራር ሁለት ቁልፍ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።

የከተማዋን ገቢ ማሳደግ ሲሆን፣ ባሕር ዳር ይህን ሁሉ ግዙፍ መሰረተ ልማት ይዛ በሀገር አቀፍ ደረጃ በገቢ አሰባሰብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ መገኘቷ የተሰሩትን ፕሮጀክቶች እንኳን ለመጠገን አቅም የሚያሳጣ በመሆኑ ነዋሪውና አመራሩ በልዩ ትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዋነኛው ጠንካራ መልዕክታቸው ደግሞ የሰላም ጉዳይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንደኛው ልጅ ጥሮ ግሮ ሲያመጣ ሌላኛው እንደሚያጠፋበት እናት ተምሳሌታዊ ታሪክ በመጥቀስ፣ "ቀኙ የሰራውን ግራ እያፈረሰው" የሚለውን ብሂል በማንሳት ያገኘነውን እድል በልማት እንድንጠቀምበት አሳስበዋል።

ልማትን ለማስቀጠል ሰላምን ማስቀደም ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበው፣ ቀኙ ግራውን ማሳረፍ ካልቻለ የተጀመሩ የልማት ተስፋዎች ሊበላሹ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

አሁን ላይ ክልሉ ራሱን በራሱ በተሟላ ሁኔታ እያስተዳደረ መሆኑን በመጠቆም፣ ሕዝቡ በጋራ በመቆም ከተማዋንና ክልሉን እንዲያለማ ጥሪ አቅርበዋል።

አለመግባባቶች ቢኖሩ እንኳ ዘመን ሳያልፍብን በጨዋነት እና በንግግር የመፍታት ባህልን ማዳበር እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው አስገንዝበዋል።

EBC

በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦችየስልታዊ ቡድኖች የምክክር ሂደትን በተመለከተሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ከባለ 10 አባላት 400 ጥቃቅን ቡድኖች ...
05/08/2026

በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

የስልታዊ ቡድኖች የምክክር ሂደትን በተመለከተ

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ከባለ 10 አባላት 400 ጥቃቅን ቡድኖች ጀምሮ ወደ ባለ 50 አባላት 80 ቡድኖች ከተሻገረ በኋላ ሰሞኑን ባለ 250 አባላት 16 ስልታዊ ቡድኖች ላይ ደርሷል፡፡

ሰሞኑን ከእያንዳንዱ ስልታዊ ቡድን የተመረጡ 25 የቃለ ጉባኤ አጠናቃሪ አባላት ከስልታዊ ቡድን አባላት እንዲሁም ከምሁራን የተሰጡ ግብዓቶችን እያካተቱ ቃለ ጉባኤቸውን ሲያዳብሩ ከርመዋል፡፡

አብዛኞቹ ባለ 250 አባላት ስልታዊ ቡድኖች ዳብሮ በቀረበው ቃለ ጉባኤ ላይ መግባበባት ፈጥረው መስማማታቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል፡፡

ጥቂት ቡድኖች የቃለ ጉባኤ ሃሳቦቻቸውን እንደገና እያስተካከሉ ወደ መጨረሻው ደረጃ ለመድረስ እየሞከሩ ነው፤ ይህ ሂደት ዛሬ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሁሉም ስልታዊ ቡድኖች ዛሬ ተስማምተው በቃለ ጉባኤቸው ላይ ከተፈራረሙ የምክክሩ ሂደት ከነገ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ጀምሮ ከስልታዊ ቡድን ወደ 500 አባላት ወዳሉት የስራ ቡድን ይሸጋገራል፡፡ የስልታዊ ቡድን ቃለ ጉባኤዎች ዛሬ ተጠናቀው ስምምነት የማይደረስባቸው ከሆነ የ500 አባላት የስራ ቡድን የምክክር ጉባኤ ወደ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ይሸጋገራል፡፡

በስልታዊ ቡድኖች ውይይት በአብዛኞቹ ቡድኖች ወደ መግባባት የሚወስድ ሀሳቦች ታይተዋል፡፡ አንዳንድ ሃሳቦች ደግሞ ማጥራትን የሚፈልጉ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ለዚህም ይህ የስልታዊ ቡድን ምክክር የፈጀውን ይፍጅ እንጂ ጥርት ብሎ ወደ ዋናው የ500 አባላት የቡድን ጉባኤ መሸጋገር እንዳለበት እየተሰራ ያለው፡፡

አመካካሪዎች፣ ምሁራንና ቃለ ጉባኤ ያዢዎችን በተመለከተ

በምክክሩ ሂደት 160 የሚደርሱ አመካካሪዎች እየተሳተፉ ነው፡፡
አመካካሪዎች የተሰጣቸውን ሚና በትክክል እየተወጡ ነው፡፡ አልፎ አልፎ አመካካሪዎችን ጨምሮ በሁሉም የምክክሩ ተዋናኞች ዘንድ ማጋደል ከታየ አይፈረድም፡፡ ነገር ግን ከአመካካሪዎች፣ ከምሁራን እንዲሁም ከኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚጠበቀው ለተመካካሪዎች ትክክለኛውን አቅጣጫ መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተመካካሪዎች የማንንም አቋም እንዲይዙ ማድረግ በፍፁም አይፈቀድም፡፡ ስለዚህ ሁሉም የምክክሩ አስፈፃሚዎች ተመካካሪዎችን በዚህ በኩል ሂዱ ብለው ከሆነ ትክክል አይደለም፤ እሱን እያጠራን ነው ያለነው፡፡ ከአመካካሪዎችና ሙያዊ ማብራሪያ ከሚሰጡ ምሁራን ጋር በየጊዜው እየተነጋገርን በአግባቡ እየመራን ነው፡፡

ምሁራን ለተመካካሪዎች ጥሩ ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሆነ እናምናለን፡፡ለዚህም እናመሰግናለን፡፡ ሆኖም የዘመሙ አካሄዶች ሲያጋጥሙ በየጊዜው እርምት እንዲደረግባቸው እያደረግን ነው፡፡

ቃለ ጉባኤ የሚይዙ ባለሙያዎች በቁጥር ከአመካካሪዎች ጋር እኩል ሲሆኑ በትልልቅ ፍርድ ቤቶች፣ በፍትህ ተቋማት፣በትምህርት ተቋማት ወዘተ የሰሩ ትልልቅ ልምድ ያላቸው አንቱ የሚባሉ ባለሙያዎች ናቸው፡፡ የሚሰሩትን ያውቃሉ፡፡ የምንነጋገርባቸውን እያንዳንዷን ነጥብ እየሰነዱ ለወደፊት እያስቀመጡ ነው፡፡

በዚህ ሂደት ውስጥ የነሱን ሀሳብ ወይም ሌሎች የሚሰጧቸውን ሃሳብ ጨምረው ያቀርባሉ የሚል እምነት የለንም፡፡

ስለ ተመካካሪዎች
ተመካካሪዎች የዳበረ እውቀትና ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ ተመካካሪዎቻችን ትልልቅ ፖለቲከኞች፣ መምህራን፣ ትልልቅ ሃላፊነት ላይ ያሉ ሰዎች፣ አርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም ሴቶችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው፤ ሁሉም የዋዛ አይደሉም፡፡ እዚህ የመጡት ለሀገር ጉዳይ ነው፡፡ ዝም ብሎ የተሰጣቸውን በሙሉ ይቀበላሉ ብላችሁ አትጠብቁ፡፡ የሚጠመዘዙም አይደሉም፡፡ በብዙ ነገሮች ላይ ንግግሮችን ቢያደርጉም ትልቁ ስዕል ግን ሀገራቸው ኢትዮጵያ መሆኗን በሚገባ ይረዳሉ፡፡

በምክክሩ ላይ የሚገኙ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ከንቲባዎችና ሚኒስትሮች እንደማንኛውም ተመካካሪ እኩል ተሳታፊ እንጂ ስልጣናቸውን የሚያሳዩበት መድረክ አይደለም።

ምክክር ማለት መከባበርና መደማመጥ እንደመሆኑ መጠን፣ የሌሎችን ማንነት ለማሳነስ ወይም ለመጨፍለቅ የሚደረጉ ጥረቶች ትክክል እንዳልሆኑና ኮሚሽኑ በሥነ-ምግባር መመሪያው መሠረት እርምጃ እንደሚወስድ ተገልጿል።

የ4000 ተመካካሪዎችን የትራንስፖርት፣ የምግብና የጤና ሁኔታ ማስተናገድ ሰፊ ስራ የሚጠይቅ ቢሆንም ሂደቱ በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ይገኛል።

በአጠቃላይ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በተቀመተለት ጊዜና የአሰራር ስነ ዘዴ እየተካሄደ ነው፤ እስካሁን የገጠመን ችግር የለም፡፡

#የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

05/08/2026

በሸካ ዞን የኪ ወረዳ በቆ ቀበሌ የተገነባው ሞዴል መንደር

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለዞን አቀፍ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ የዕቅድ አፈፃፀም ማጠቃለያና...
05/08/2026

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ

ዞን አቀፍ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስራ የዕቅድ አፈፃፀም ማጠቃለያና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።

በመድረኩ የሸካ ዞን ሰላም፣ ፀጥታና ሚሊሻ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዋስሁን አውሎ እንደገለፁት ወሳኝ ኩነት በመንግስት ትኩረት ሰጥቶት የሚሰራ መሆኑን ገልፀው እስከ ቀበሌ መዋቅር ድርስ በተቀናጀ መልኩ ሊተገበር እንደሚገባ ተናግረዋል።

በዲጂታል ሲስተም በመታገዝ ምዝገባ መፈፀም፣ሪፖርት በወቅቱ ማቅረብ፣ባለሙያዎች በስነ-ምግባርና በቅንጅት ሊሰሩ ይገባልም ብለዋል።

በቀጣይ እያንዳንዱ ኩነቶች ሙሉ በሙሉ በሚመዘገቡበት ሂደት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በዘላቂነት እንዲሠሩ አሳስበዋል።

በዞኑ የወሳኝ ኩነት ቡድን መሪ አቶ ሰለሞን ጋሪፎ የወያያ ሰነድ ቀርቦ በአፈፃፀሙና ለቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በበጀት ዓመቱ በአምስቱም መዋቅሮች የተሻለ አፈፃፀም ያለመኖሩን ገልፀው ለዚህ ተግዳሮት የሆነው ሪፖርት በወቅቱ ያለማቅረብ፣ዲጂታል ምዝገባ በተግባር ያለመፈፀም ክፍተቶች ለአፈፃፀሙ ተግዳሮት መሆኑ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በወሳኝ ኩነት ምዝገባና ብሔራዊ መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 760/2004 እና በአዲሱ የሲቪል እና ቤተሰብ አዋጅ ቁጥር 1370 ተሻሽሎ የቀረበ አንቀጽም ይፋ ተደርጓል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሪፖርቱ ለቀጣይ ስራቸው የሚያነቃቃና የተሻለ መሆኑን ገልፀው የሲስተም ችግር፣በወቅቱ ዕቅድ ያለማዘጋጀት፣የእድሜ ማጭበርበር ችግሮች መኖራቸውን ገልፀው ለቀጣይ ይህን በመቅረፍ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም ተናግረዋል።

ዘጋቢ:ምንታምር አስፋው

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለ...
05/08/2026

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ

ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።

እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።

የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።

ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።

የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።

የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።

ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።

Address

Sheka Zone
Masha
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sheka TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category