13/08/2026
የደቡብ ኦሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ በ2018 ዓ.ም አፈፃፀምና በ2019 ዓ.ም በጀት አመት እቅድ ዙርያ ውይይት አደረገ
ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም (የደቡብ ኦሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ-ዲመካ)
የደቡብ ኦም ዞን ቱሪዝም መምሪያ በ2018 ዓ.ም አጠቃይ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም እና የ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ዙርያ የመምሪያው ኃላፊ አቶ አጉሞ ሎኮርዮ እና አጠቃላይ ሠራተኛ በተገኘበት ተወያይቷል።
በምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ተቋሙ በጠንካራና ደካማ ጎኖች ዙርያ በተገመገመበት ወቅት እንዲሁም የዞኑ ፐብልክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ በቢሮው በመገኘት ባደረጉት የምዘና ሂደት ውሰጥ መምሪያው በሪፈርም ስራ የተሻለ አፈፃፀም እንዳለው የተገመገመ ሲሆን እንደ ክፍተት በዓመቱ ከህዝብ ክንፍ ጋር ውይይቶች አለመደረጋቸው እንደ ክፍተት የታየ በመሆኑ በቀጣይ በቋሚነት በየሩብ ዓመቱ ከህዝብ ክንፍ ጋር ውይይት ለማድረግ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በ2019 ዓ.ም በጀት አመት ተቋማዊ የማስፈፀም አቅምን በማሻሻል የአገልግሎት አሰጣጥን ማሣደግ እንደሚገባ ፣የዞኑን የቱሪዝም አለኝታዎች በመለየት መዳረሻዎችን ማልማትና ማስፋፋት፣የፕሮሞሽንና ግብይት ስራዎችን በማጎልበት የጎብኚዎችን ፍሰት መጨመር እንደሚገባ በውይይት ወቅት የተነሱ ሀሳቦች ናቸው። በዞኑ የሚገኙ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጥራታቸውን በማሣደግ ቱሪዝም ለዞኑ እየሠጠ ያለውን የኢኮነሚ ድርሻ በተገቢው እንዲወጣ ለማድረግ መስራት እንደሚገባም መግባባት ላይ ተደርሷል።
በውይይቱ ማጠቃላያ የቢሮ መግብያና መውጫ ሰዓትን በማክበር፣የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን እንዱሁም የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መስራት እንደሚገባ የመምሪያው ኃላፊ አሳስበዋል።