Legga Media

Legga Media የእውነተኛ የመረጃ ቻናል ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ ለማስታወቂያ ክፍት ነው በ 0911145988 ሀሰብ አስታየትዎን ያጋሩን 🙏
(3)

13/06/2026

ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ቤተሰብና ድረሱላቸው 🙏
የትዕግስት ልክ ናት አንጀቴ የተላወሰው ተመልከቱት

ሼር ለሁሉም ይድረስ
Legga Media

13/06/2026

አክቲቪት ስታሊን ደብረጽዮንን ወረደበት እስቲ አድምጡት
ሼር

ዶሮው ታማበት ወደ ሰዎች መታከሚያ ሆስፒታል ይዞ የሄደው ታዳጊ የ100 ዶሮዎች ስጦታ ሊበረከትለት ነው። ከቀናት በፊት ዶሮው ስትታመምበት ፍቅሩና የዋህነቱ አስገድዶት ወደ ሰዎች ሆስፒታል ይዞ...
13/06/2026

ዶሮው ታማበት ወደ ሰዎች መታከሚያ ሆስፒታል ይዞ የሄደው ታዳጊ የ100 ዶሮዎች ስጦታ ሊበረከትለት ነው።

ከቀናት በፊት ዶሮው ስትታመምበት ፍቅሩና የዋህነቱ አስገድዶት ወደ ሰዎች ሆስፒታል ይዞ በመምጣት ማህበራዊ ሚዲያውን መነጋገሩ አይዘነጋም የገጠሩ ታዳጊ ታሪክ አሁን ላይ ፍጹም አዲስና አስደሳች መልክ ይዟል።

ይህ የልብ ንጽህናውና የእንስሳት አጠባበቅ ጥንቃቄው መገለጫ የሆነው ልብ የሚነካ ታሪክ በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት ከተሰራጨና የብዙዎችን ቀልብ ከሳበ በኋላ፣ በርካታ ድርጅቶችና በጎ አድራጊዎች ታዳጊውን ለመደገፍና ለማበረታታት በይፋ መነሳት ጀምረዋል።

የታሪኩን መሰራጨት ተከትሎ ለታዳጊው የወደፊት ህይወትና ስራ ልዩ ልዩ ድጋፎችን ለማድረግ ቃል እየገቡለት የሚገኙ ተቋማት ቁጥር እየጨመረ የመጣ ሲሆን....

በተለይም አግሮ ትረስት (Agero farm Trust consulting ) የተባለው ድርጅት የወጣቱን ጠንካራ ተነሳሽነት ለመደገፍ 100 ዶሮዎችን በስጦታ ለማበርከት ቃል ገብቷል።

ታዳጊው መጀመሪያ ላይ የታመመችውን ዶሮውን ይዞ ወደ ሆስፒታል በሄደበት ወቅት በርካታ ሰዎች በድርጊቱ ላይ እንደተሳለቁበትና እንዳፌዙበት የገለጸ ቢሆንም....

አብሮት የነበረው ሰው ግን የሰዎችን ማሾፍ ወደ ጎን በመተው በውስጡ ያለውን የልብ ቅንነትና ንጹህ ሰብአዊነት ብቻ እንዲመለከት መምከሩን ግዮን ማለዳ ከቪዲዮው ተመልክቷል ።

አሁን ላይ የተገኘው ወገንተኝነትና የድርጅቶች አጋርነት የቅንነት ዋጋ ፈፅሞ እንደማይጠፋ ያሳየ ትልቅ ማሳያ ሆኗል።

via ግዮን ማለዳ

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሀገርን ስም የሚያስጠሩ ስፖርተኞችን የማፍራት ተግባሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሀገርን ሰንደቅ ...
13/06/2026

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሀገርን ስም የሚያስጠሩ ስፖርተኞችን የማፍራት ተግባሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አቀፍ መድረኮች ከፍ አድርገው የሚያውለበልቡ እውቅ አትሌቶችንና ስፖርተኞችን የማፍራት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ ገለጹ።

ሚኒስትሯ ይህን የተናገሩት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረቱበትን 40ኛ ዓመት በዓል ባከበሩበት መድረክ ላይ ነው።

በመድረኩ ለታዋቂዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ የተሰጠ ሲሆን፤ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ በስፖርት ክለቡና በኪነ-ጥበብ ቡድኑ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ዕውቅና ተሰጥቷል።

የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት በሀገሪቱ የስፖርት ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ማሳረፉን ገልጸዋል።

የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አቀፍ መድረኮች ከፍ ያደረጉ እውቅ አትሌቶችንና ስፖርተኞችን በማፍራት በኩል ተቋሙ የተጫወተው ሚና የላቀ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኮሚሽኑ በስፖርትና በኪነ-ጥበብ ዘርፍ የጀመራቸውን አበረታች ሥራዎች ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ በፍርድ ቤት ውሳኔ የሚላኩ ታራሚዎችን አምራችና ሕግ አክባሪ ዜጋ አድርጎ የማውጣት ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት የተጣለበት ተቋም መሆኑን አስታውቀዋል።

ይህን ኃላፊነት ለመወጣት በሚያደርገው ጥረት የስፖርት ክለቡ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ የሕግ ማረም ሥራውን በጥበብና በማስረጽ፣ እንዲሁም በስፖርት የአካል ብቃት በማጎልበት ታራሚውን እያዝናኑና እያስተማሩ በመቅረጽ በኩል ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል።

ሁለቱም ክፍሎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተለይም የስፖርት ክለቡ በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ መድረኮች የሀገርን ስም ያስጠሩ በርካታ ጀግና ስፖርተኞችን ያፈራ መሆኑን ገልጸዋል።

በአትሌቲክሱ ዘርፍ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊትና ጥቁር ሴት የኦሎምፒክ ሻምፒዮን የሆነችውን ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉን፣ ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን፣ አትሌት ስለሺ ስህን እንዲሁም የማራቶን ጀግናዋን ፋጡማ ሮባን ማፍራቱን በኩራት አስታውሰዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ በኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ውስጥ ጎልቶ የሚታይ ደማቅ አሻራ ያሳረፉና ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ በርካታ የጥበብ ባለሙያዎችን ለሀገር ማበርከቱን ጠቁመዋል።
ኢዜአ

አቶ በላይ ባልጉዳ ሀዋሳን የፌዴራል መንግስት ተጨማሪ መቀመጫ ለማድረግ የሚሰራውን ስራ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ለሚነሱ ትችቶች ምላሽ ሰጡየሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ...
13/06/2026

አቶ በላይ ባልጉዳ ሀዋሳን የፌዴራል መንግስት ተጨማሪ መቀመጫ ለማድረግ የሚሰራውን ስራ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ለሚነሱ ትችቶች ምላሽ ሰጡ

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፖለቲካው ከወሰነ ሀዋሳን የፌደራል መንግስት ተጨማሪ መቀመጫ ለማድረግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው በማለት ያደረጉትንነረግግር ተከትሎ፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ለሚሰነዘሩ ትችቶችና አስተያየቶች አቶ በላይ ምላሽ ሰጥቷል።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባል፣ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አመራርና የቀድሞ የኤጄቶ አባል የሆኑት አቶ በላይ ባልጉዳ በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ የከተማዋን እድገት የማይፈልጉ አካላትን አጥብቀው ወቅሰዋል።
አቶ በላይ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ የክልሉ መንግስት በሀዋሳ ከተማ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች እና አምስት ኤምባሲዎች ቢሮዎቻቸውን እንደሚከፍቱ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የሚሰነዘሩ ተቃውሞዎችን የእብደት መልክ ያላቸው ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

ሀዋሳ የፌዴራል መንግስት ተጨማሪ መቀመጫ መሆኗና የዲፕሎማቲክ ተቋማት መግባት ይዘውት የሚመጡትን ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ያስረዱት አቶ በላይ፣ የዚህ ውሳኔ ቀጥተኛ ውጤት ለሲዳማ ህዝብ ሰፊ የገበያ ዕድልና የኢኮኖሚ መነቃቃትን የሚጨምር መሆኑን አስገንዝበዋል።

የከተማዋን እድገትና ልማት የሚቃወሙ ኃይሎችን ድንቁርና የተጠናወታቸው ሲሉ የገለጹት የምክር ቤት አባሉ፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ታቅበው አደብ እንዲገዙ ጥሪ አቅርበዋል።

አያይዘውም ከእንዲህ አይነቱ አስተሳሰብ ውጪ በድንቁርና ልማትና ዕድገትን ማረጋገጥ እንደማይቻል በአፅንኦት አሳስበዋል።

ዘግቦታል

በሀድያ ዞን ያለምክንያት የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 347 ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደበሀድያ ዞን ያለምክንያት በሸቀጣሸቀጥ፣ በጥራጥሬ እንዲሁም ምግብና ምግብ ነክ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ...
13/06/2026

በሀድያ ዞን ያለምክንያት የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 347 ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

በሀድያ ዞን ያለምክንያት በሸቀጣሸቀጥ፣ በጥራጥሬ እንዲሁም ምግብና ምግብ ነክ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 347 ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

በጥሬ ገንዘብ ከተጣለው ቅጣትም በጥቂት ቀናት ውስጥ ከ375 ሺህ ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ተከተል ዶባሞ ለሀድያ ቴሌቪዥን በሰጡት መረጃ፤ እርምጃው የተወሰደው በዞኑ እየተደረገ ባለው የዋጋ ቁጥጥር ሥራ የዋጋ ዝርዝር ሳይለጥፉና መሠረታዊ ባልሆነ ምክንያት የዋጋ ጭማሪ በማድረግ በሸማቹ ላይ የኑሮ ጫና ሲፈጥሩ በተገኙ የንግድ ቤቶች ላይ ነው።

ከዚህ ባለፈም የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው በመንገድ ላይ በሚነግዱ አካላት ላይ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

ይህን በኅብረተሰቡ ላይ የሚስተዋለውን የኑሮ ውድነት ችግር ለመቅረፍ በዞኑ ልዩ የ20 ቀን ዕቅድ መዘጋጀቱን ኃላፊው ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት፦የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የነዳጅ አቅርቦት ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የዋጋ ንረትንና ሕገወጥነትን የሚከታተል ግብረኃይል በማቋቋም ቁጥጥሩን ማጠናከር፣ሕገወጥ ንግድን ሥርዓት ማስያዝ የሚሉ ዋና ዋና ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኑሮ ውድነቱን ጫና በዘላቂነት ለመቀነስ የሰንበት ገበያዎችን የማጠናከርና የማስፋት ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን የገለጹት አቶ ተከተል፤ ይህም አምራቾችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገናኙበትን ዕድል በመፍጠር ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው ብለዋል።

ይህ የቁጥጥርና የሕግ ማስከበር ሥራ ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ባሉ አመራሮች ቅንጅት እየተመራ የሚገኝ በመሆኑ፣ አጠቃላይ የዞኑ ማኅበረሰብ ለሥራው ስኬታማነት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ መምሪያው ጥሪ አቅርቧል።

via HTV

13/06/2026
ከ 5 መቶ ሺ በላይ የተለያዩ  #ችግኞችን ያዘጋጀው ወጣትበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ድንጋይን ወደ አረንጓዴነት በመቀየር በኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ላይ ከፍተኛ አሻራ...
13/06/2026

ከ 5 መቶ ሺ በላይ የተለያዩ #ችግኞችን ያዘጋጀው ወጣት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ድንጋይን ወደ አረንጓዴነት በመቀየር በኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ላይ ከፍተኛ አሻራ እያስቀመጠ ይገኛል ወጣት ዘውዱ ጡምደዶ።
የወጣት ዘውዱ የችግኝ ማዕከሉ ምድራዊ ገነት ይመስላል።
ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠንሳሽነት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ኢኮኖሚ በአፍሪካ ብሎም በአለም ግንባር ቀደም ሚና እየተወጣች ትገኛለች።
ለዚህ ተግባር ውጤታማነት ሁሉም ዜጋ የራሱን ድርሻ መወጣት የሚጠበቅ ነው።እንደ ሀገር ለአረንጓዴ አሻራ ልማት የሚሆኑ የተለያዩ የእጽዋት ችግኞችን በማፍላት የአንበሳውን ድርሻ እየተወጡ ከሚገኙ ከኢትዮጵያ ወጣቶች አንዱ ወጣት ዘውዱ ጡምደዶ ነው።

ወጣት ዘውዱ ጡምደዶ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና እንዲሁም የሀዲያ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ሆሳዕና ከተማ በሴች ዱና ቀበሌ ዘውዱ ጡምደዶ ሀርባን ጋርደን በተሰኘው የችግኝ ማዕከል የተለየዩ ለምግብነት፣ለመድኃኒትነት ፣ለውበት እና ለጥላ የሚያገለግሉ ችግኞችን በማፍላት ለአካባቢው እና በሀገሪቱ ለተለያዩ ክልሎች በማሰራጨት ይገኛል።
ወጣት ዘውዱ ይህን የችግኝ ማዕከሉን ወደ አረንጓዴነት የቀየረው ከዚህ ቀደም ድንጋያማ እና አረንጓዴ ይሆናል ተብሎ የማይታሰብ መሬት ነበር።ታዲያ ወጣት ዘውዱ ማዕከሉን የቱሪስት መስህብነት በሚውልበት መልኩ ያየውን ሁሉ የሚማርኩ የተለያዩ ለምግብነት፣ለመድኃኒትነት፣ለውበት እና ለጥላነት የሚውሉ የአትክልት፣የፍራፍሬ፣የዛፍና የአበባ ችግኞችን በማፍላት በሀገር አቀፍ ደረጀ በማሰራጨት ላይ ይገኛል።
ወደዚህ ችግኝ ማዕከል መጥተው አጥተው የሚመለሱ የችግኝና የአበባ አይነት አይኖርም።
አድራሻችን ሆሳዕና ከተማ በሶሮ መውጫ ገረገንቲ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ እንገኛለን።
ከወጣት ዘውዱ የችግኝ ማዕከል የፈለጉትን የችግኝ አይነት ማግኘት ከፈለጉ ባሉበት ሆነው በስልክ ቁጥሮቻችን
0913637663 አልያም በ0924695073 ደውለው ማግኘት ይችላሉ።
ዘውዱ ጡምደዶ ሀርባን ጋርደን የችግኝ ማፊያ ማዕከል
ሆሳዕና
Abiy Ahmed Ali

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) መልዕክትየአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት ላይ እንገኛለን። ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ  በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነ...
13/06/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት ላይ እንገኛለን። ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል!

Address

Seche Duna
Hossana
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Legga Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Legga Media:

Share

Category