Legga Media

Legga Media የእውነተኛ የመረጃ ቻናል ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ ለማስታወቂያ ክፍት ነው በ 0911145988 ሀሰብ አስታየትዎን ያጋሩን 🙏

በዳውሮ ዞን በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር ሲያሰራጭ የነበረ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ​በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር ሲያሰራጭ የነበረ...
16/08/2026

በዳውሮ ዞን በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር ሲያሰራጭ የነበረ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

​በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር ሲያሰራጭ የነበረ ግለሰብ በጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

​የዳውሮ ዞን ፖሊስ መምሪያ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ዲቪዥን ክፍል ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር አሰራት ዶግሶ እንደገለጹት፣ ተከሳሹ ማቴዎስ ባቡሎ በየኔ የተባለ ግለሰብ በማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም በኦርቶዶክስ እና በፕሮቴስታንት ሃይማኖት ተከታዮች መካከል መቃቃር እና ጥላቻ እንዲፈጠር የሚያደርጉ የጥላቻ ንግግሮችን ሲያሰራጭ ተደርሶበታል።

​የቀረበውን የወንጀል መዝገብ እና ማስረጃ የተመለከተው የማሪ ማንሳ ወረዳ ፍርድ ቤት በተከሳሹ ላይ የተሰነዘረውን የጥላቻ ንግግር ወንጀል መረጋገጡን ተከትሎ፣ ተከሳሽ ማቴዎስ ባቡሎ በየኔ በአንድ ዓመት ከሁለት ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።

​ፖሊስ አክሎም ህብረተሰቡ ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ ብቻ እንዲጠቀም እና በሃይማኖቶች መካከል ልዩነት እና ግጭት የሚፈጥሩ ድርጊቶችን ከመፈጸም እንዲቆጠብ አሳስቧል።

"ከባባድ መሳሪያዎች ከኤርትራ ትግራይ እንደገቡ አውቃለሁ" - አሜሪካየአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ጋር በስልክ ተወያይተዋል።📌 የአምባሳደሩ ማስጠንቀቂ...
16/08/2026

"ከባባድ መሳሪያዎች ከኤርትራ ትግራይ እንደገቡ አውቃለሁ" - አሜሪካ

የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ጋር በስልክ ተወያይተዋል።

📌 የአምባሳደሩ ማስጠንቀቂያ፡ አምባሳደር ማሲንጋ ለዶክተር ደብረጽዮን “የሸረሪናውን ውጊያ እናንተ ናችሁ የጀመራችሁት” በማለት ሕወሓትን ወቅሰዋል።

📌የዲፕሎማሲ ትችት፡ “ዲፕሎማሲን የጣላችሁ እና ያዳከማችሁ እናንተ ናችሁ” ያሉት አምባሳደሩ፣ በቅርቡ በሕዝባዊ ስብሰባዎች ላይ የተንጸባረቁ ጠንካራ ንግግሮችንም ኮንነዋል።

📌ከባባድ መሳሪያዎች፡ አምባሳደሩ በቅርቡ ታንኮችና መድፎች ከኤርትራ ወደ ትግራይ መግባታቸውን አሜሪካ እንደምታውቅ አስታውቀዋል።

📌የሕወሓት ስብሰባ፡ ዶክተር ደብረጽዮን ይህን የውይይት ዝርዝር በቅርቡ በተካሄደው የሕወሓት ፖሊት ቢሮ ስብሰባ ላይ ሪፖርት ማድረጋቸው ታውቋል።

"አህያና ውሻ አብረው ጉዞ ይጀምራሉ። ሁለቱም እጅግ ርቧቸው ስለነበር፣ አቅም አጥተው በቀስታና በዝምታ ይጓዛሉ። ከተወሰነ ርቀት በኋላ ለም ሳር ያለበት ቦታ ላይ ደረሱ። አህያው ሳሩን በደስታ...
16/08/2026

"አህያና ውሻ አብረው ጉዞ ይጀምራሉ። ሁለቱም እጅግ ርቧቸው ስለነበር፣ አቅም አጥተው በቀስታና በዝምታ ይጓዛሉ። ከተወሰነ ርቀት በኋላ ለም ሳር ያለበት ቦታ ላይ ደረሱ። አህያው ሳሩን በደስታ እየጋጠ ሲበላ፣ ወዲያው ጉልበቱ ተመለሰለት። አመሻሽ ላይ አህያው ሆዱ እስኪወጠር ድረስ በጣም ጠገበ። አህያው ን"ኧረ ባክህ ውሻው... አንድ ጊዜ ልጩህ?" ብሎ ጠየቀው። ውሻውም ደንግጦ " አርፈህ ተቀመጥ! ድምጻችንን ሰምቶ ጅብ ይመጣብናል!" ሲል አስጠነቀቀው።...
አህያው ግን በጥጋብ ስለሰከረ አልሰማውም። መሬቱ ላይ ተንከባሎ በኃይል ጮኸ። ውሻው "እባክህ እረፍ! ጥጋብ መዘዝ ያመጣብናል!" ቢለውም፣ አህያው አልሰማውም፤ ሁለተኛም ደገመው።..
ብዙ አልቆየም... የጮኸውን ድምፅ የሰማው ነብር ከየት መጣ ሳይባል ከፊታቸው ከተፈ። ነብሩም ም አህያውን ወዲያውኑ ይዞ ዘረረው። ከዚያም ውሻውን "እስኪ አህያውን በልትልኝ" ብሎ አዘዘው።..
ውሻውም በጣም ርቦት ስለነበር አህያውን እየበለተ፣ ልቡን አውጥቶ በላው። ነብሩ ምግቡን ለመብላት ሲቀርብ አስተዋለና "ለመሆኑ የዚህ አህያ ልቡ የት አለ?" ብሎ ውሻውን ጠየቀው። ውሻውም ቀና ብሎ "ጌታዬ... ልብ ቢኖረውማ በዚህ ሰዓት ይጮህ ነበር?!" አለው ይባላል።...
ጥጋብና ስኬት በመጣ ጊዜ ልብንና አእምሮን ማጣት መዘዝ ያመጣል። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነን ጊዜውን፣ ቦታውንና አካባቢያችንን አስተውለን መንቀሳቀስ ያስፈልጋል።"
መልዕክት አለዉ!!

ዛሬ የሚደረገው ታሪካዊው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ፍልሚያየ2026/27 የእንግሊዝ እግር ኳስ ውድድር ዘመን በይፋ መጀመርን የሚያበስረው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ 11 ሰአት ላይ በአርሰናል ...
16/08/2026

ዛሬ የሚደረገው ታሪካዊው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ፍልሚያ

የ2026/27 የእንግሊዝ እግር ኳስ ውድድር ዘመን በይፋ መጀመርን የሚያበስረው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ 11 ሰአት ላይ በአርሰናል እና ማንቸስተር ሲቲ መካከል ይካሄዳል።

የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ እ.ኤ.አ. በ1898 ከነበረው የለንደን ሸሪፍ የበጎ አድራጎት ዋንጫ ተነስቶ የዛሬውን ዘመናዊ ይዘት እንደያዘ ይነገራል።

የመጀመሪያው ጨዋታ በ1908 በማንቸስተር ዩናይትድ እና በኩዊንስ ፓርክ ሬንጀርስ መካከል ተካሂዶ ዩናይትድ 4 ለ 0 በማሸነፍ የመጀመሪያው አሸናፊ ሆኗል።

በ1974 በቴድ ክሮከር ጥረት በየዓመቱ በዌምብሊ ስታዲየም በሊጉ ሻምፒዮን እና በኤፍኤ ካፕ አሸናፊ መካከል እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን በ1993 የፕሪሚየር ሊጉን መመስረት ተከተሎም የውድድር ዘመኑ ትልቅ መክፈቻ ሆኖ ቀጥሏል።

ከዚህ ቀደም "ቻሪቲ ሺልድ" በመባል የሚታወቀው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ከትኬት እና ዝግጅቱ የሚገኘው ገቢ በእንግሊዝ ለሚገኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ለማኅበረሰብ ልማት ፕሮጀክቶች የበጎ አድራጎት ዓላማ ይውላል።

ይህ ተጠባቂ ጨዋታ በግዙፉ ዌምብሊ ስታዲየም ቀደም ሲል በተያዙ የኮንሰርት መርሃ ግብሮች ምክንያት የዛሬው ፍልሚያ ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ካርዲፍ በመመለስ በፕሪንሲፓሊቲ ስታዲየም ይከናወናል።

በሁለቱ ክለቦች መካከል በኮሚዩኒቲ ሺልድ ታሪክ ያለው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ በሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የበላይነት የተያዘ ነው። ሁለቱ ቡድኖች በውድድሩ (በ1934፣ በ2014 እና በ2023) 3 ጊዜ ሲገናኙ መድፈኞቹ ሶስቱንም ማሸነፍ ችለዋል።

ከፔፕ ጓርዲዮላ ጋር በመለያየት በአዲሱ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ለሚመራው ሲቲ፣ ዋንጫውን ማሸነፍ ከአዲሱ አሰልጣኝ ጋር የድል መንገድ መጀመሩን ለማሳየት እና ታሪካዊ ብልጫውን ለመቀየር ትልቅ እድል ነው።

ለወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ደግሞ ውድድሩን በድል መጀመር የበላይነቱን ለማስጠበቅ እና ለቀጣዩ የፕሪሚየር ሊግ ጉዞው ጠንካራ የስነ-ልቦና መነቃቃትን ይፈጥርለታል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህንን የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ በታሪክ ብዙ ጊዜ በማንሳት ማንቸስተር ዩናይትድ በ21 ዋንጫዎች ሲመራ፣ አርሰናል በ17፣ ሊቨርፑል በ16 ፣ ኤቨርተን በ9 እንዲሁም ማንቸስተር ሲቲ እና ቶተነሀም ሆትስፐርስ በ7 ይከተላሉ።

የኮሚዩኒቲ ሺልድ አሸናፊ መኾን አንዳንዴ በሊጉ ስኬታማ ላለመኾን በእግር ኳስ አፍቃሪያን ዘንድ እንደ እርግማን ሲቆጠር ይታያል።

በእንግሊዝ ፕርምየር ሊግ ​ባለፉት 16 ዓመታት የኮሚዩኒቲ ሺልድ እና የፕሪምየር ሊግ ዋንጫዎች ማሸነፍ የቻለው እ.ኤ.አ በ2018/19 ማንችስተር ሲቲ ብቻ ነበር።

ለዚህም ምክነያት በፕሪምየር ሊጉ ታሪክ ከ1992 ወዲህ ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በስምንት አጋጣሚዎች ብቻ መሆኑ ነው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ያደርጋል************************ የባህር ዳር ስታዲየም በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ጊዜያዊ ፍቃድ ...
16/08/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ያደርጋል
************************

የባህር ዳር ስታዲየም በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ጊዜያዊ ፍቃድ ማግኘቱን ተከትሎ፤ መስከረም ወር ላይ የሚያደርገውን የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ማድረግ እንደሚያስችለው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በቅርቡ በባህር ዳር ስታዲየም ላይ ያደረገውን ፍተሻ እና ግምገማ ተከተሎ ብሔራዊ ቡድናችን በመስከረም ወር 2019 በሜዳው ለሚያደርገው ጨዋታ የሚያገለግል ጊዜያዊ የካቴጎሪ 3 (CAT 3) ፈቃድ መስጠቱን ነው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በላከው ደብዳቤ ያሳወቀው።

ካፍ በስታዲየሙ የተመዘገቡ መሻሻሎችን በማድነቅ በላከው ደብዳቤ አሁንም ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ያልተጠናቀቁ ጉዳዮች እንዳሉ ገልጿል። የተቆጣጣሪ ቡድኑን ግኝቶች እና የሚቀሩ የማስተካከያ እርምጃዎችን የያዘ ሙሉ ቴክኒካዊ ሪፖርት በቅርቡ ለፌዴሬሽኑ እንደሚላክም ገልጿል።

ጨዋታው በሚደረግበት ቀን የስታዲየሙን ዝግጁነት እና የደንቦች አተገባበር ለመከታተል የስታዲየም ተቆጣጣሪ ሊመድብ እንደሚችልም ካፍ አስታውቋል።

በሶማሊያ የ46ኛ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ተልዕኮውን አጠናቆ ቀጠናውን ለተተኪው ሻለቃ አሥረከበ።የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በሶማሊያ በሠላም ማሥከበር ተልዕኮ ግዳጅ...
16/08/2026

በሶማሊያ የ46ኛ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ተልዕኮውን አጠናቆ ቀጠናውን ለተተኪው ሻለቃ አሥረከበ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

በሶማሊያ በሠላም ማሥከበር ተልዕኮ ግዳጅ ላይ የቆየው 46ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አሥከባሪ ሻለቃ ቆይታውን አጠናቆ ቀጠናውን ለተተኪው 1ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አሥከባሪ ሻለቃ አሥረክቧል።

የ46ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል ሞላ ሹመት ላለፉት ሶስት ዓመታት የሠላም ማስከበር ተልዕኮውን ሲወጣ የቆየው ሻለቃው የአልሸባብን ተለዋዋጭ ባህሪ በመረዳት ጠላት ከሚያስበው በላይ ሆኖ በመገኘታችን በተሠጠን ቀጠና አሰተማማኝ ሰላም እንዲሠፍን የሚያደርግ ሥራ ሠርተናል ብለዋል።

ከአካባቢው ህዝብ የመንግስት አመራሮች የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በጋራ በመስራት ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ቀድመን በመድረስ ሠራዊቱ የኔ ነው የሚል አሰተሳሰብ ፈጥሮ ህዝባዊነቱን ማረጋገጥ ችሏልም ሲሉ ተሞክሯቸውን አሥተላልፈዋል።

የተረካቢው የ1ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል መንገሻ ታከለ በበኩላቸው ከወሰድነው ስልጠና እና ልምድ ተጨማሪ ግብዓቶችን እና ተሞክሮዎችን ከ46ኛ ሻለቃ ማግኘታችን በቀጣይ ተልዕኳችንን በጠንካራ አፈፃፀም ለመወጣት ያሥችለናል ብለዋል።

የሚገጥመንን ግዳጅ በአስተማማኝ ለመመከት ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ መሥራትና ህዝባዊነታችንን ማጉላት ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ህዝብ ሠላም የምትተጋ መሆኑን በተግባር ማሳየትና የአልሸባብን እንቅስቃሴ በቅርብ መከታተል ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው ሲሉ ኮሎኔል መንገሻ ታከለ አሥገንዝበዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

16/08/2026

አቶ ጌታቸው ረዳ ያወጣው የህወሓት ሚስጥር ሙሉውን ተመለከቱ

Legga Media

16/08/2026

ኦሌ ኦሎሌ
AI

15/08/2026

ይህን ድንቅ ምክር አድምጡ 🙏

 #የጠምባሮ ኦሞ ወንዝ የተፈጥሮ ውብ ስፍራ የብርቅዬ እንስሳት መገኛ ልዩ ምድር።Legga Media
15/08/2026

#የጠምባሮ ኦሞ ወንዝ የተፈጥሮ ውብ
ስፍራ የብርቅዬ እንስሳት መገኛ ልዩ ምድር።

Legga Media

Address

Seche Duna
Hossana
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Legga Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Legga Media:

Shortcuts

Share

Category