24/10/2025
...‼️
ለፍርድ እንዲቀርብ ያጨነው፣ ለድርድር ቀርቦ ሲያወራን፤
ስለ አንድነት ስንሰበክ፣ ልዩነትን እያወሳን፤
ጡት አጥብተው ያሳደጉን፣
ያልወለዱን እናቶችን፣ ፍቅራቸውን እየረሳን፤
እንደ ጆሮ ቆራጭ ታሪክ፣
ጡት ቆራጩ የሚል ተረት፣ በልጆች ፊት እያነሳን፤
ጥላቻና ቂም ወለድን!
እርቅ ፈርተን፣ ፀብ ወደድን!
መረዳዳት ፈራን፣ እየተራረድን!
ፍቅር ፈራን!
እርቅ ጠላን እንዳንድን!
#ፈራን እምነት ፈራን...!
የለውጡ ሀይል ሲመጣ፣ በቃሉ ያሳመነንን፤
አንዱ አሳዳጅ አንዱ ተሳዳጅ፣ ከእንግዲህ አይሆንም ያለንን!
ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው፣ ተረኛ ነኝ ባይ ሲያሳደን፤
አንደኛው በዚህ ሲያግተን፣ አንዱ ደግሞ በዚያ ሲያርደን፤
በሞትና በሞት መሃል፣ አንድ ህይወታችንን ጥደን፤
አንድ አምላክን እየጠራን!
እምነት ፈራን!
ወደ ህይወት ስንጠራ፣ ወደ እልቂት እያመራን!
መደመርን ፈራን!
አንድነትን ፈራን!
አብሮ መጓዝ ፈራን!
እውነት ፈራን!
ሰው መሆን ፈራን!
ዘር ማንዘሮች እየዘራን!
፣ ጥላቻችን እየመራን፤
ፈውስ ፈራን....
የመዳን ቃል የሚነግረን፣ ስለ ሟቾች እያወራን!!!