VisitArbaminch

VisitArbaminch ህይወት አጭር ናት አርባምንጭን ሳትጎበኙ እንዳትሞቱ❤️

«ዮ__ማስቃላ» የጋሞ ብሄረሰብ የዘመን መለጫ በዓልበጋሞ ዞን በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀውን «ዮ ማስቃላ» የዘመን መለወጫ በዓልን በድምቀት ለማክበር ሁሉም በየፈርጁ ዝግጅቱን ቀደም ብሎ ይጀም...
21/08/2026

«ዮ__ማስቃላ»
የጋሞ ብሄረሰብ የዘመን መለጫ በዓል
በጋሞ ዞን በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀውን «ዮ ማስቃላ» የዘመን መለወጫ በዓልን በድምቀት ለማክበር ሁሉም በየፈርጁ ዝግጅቱን ቀደም ብሎ ይጀምራል።
«ዮ ማስቃላ» በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ቅበላው ተከብሮ በታህሳስ ወር መጨረሻ የ«ማስቃላ» ሽኝት በዓል በድጋሚ በድምቀት ይከበራል።
በዞኑ በተለያዩ ማህበራት በመደራጀት ገንዘብ የማሰባሰብ ዝግጅት የሚጀምሩት ቀደም ብሎ ነው። በዚሁ መልኩ ዓመቱን ሙሉ ገንዘብ በመቆጠብ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ይደረጋል።
ይህ ተግባር በሁለቱ ፆታዎች የሚከናወን ዝግጅት ሲሆን ወንዶች ለበዓሉ የሚሆን ሠንጋ መግዣ፣ ለልጆች ልብስ እና ጌጣጌጥ ማሟያ፤ እናቶች ደግሞ በበኩላቸው ለቅቤ፣ ለቅመማ ቅመም፣ ለባህላዊ ምግቦች እና መጠጦች እህል መግዣ የሚሆን ገንዘብ ማጠራቀም ያጠራቅማሉ።
ለማስቃላ በዓል የሚዘጋጁ ተወዳጅ ባህላዊ ምግቦች መካከል የገብስ ቅንጬ፣ ከቡላ ቆጮ እና ገብስ የሚዘጋጅ ቂጣ፣ የቡላ ፍርፍር፣ የሐረግ ቦዬ ሲሆኑ ቦርዴ፣ የማርና የቦርዴ ውህድ የመሳሰሉ ባህላዊ መጠጦችም በስፋት ይዘጋጃሉ።
በጋሞ ዞን የማስቃላ በዓል ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንሳስት እና ለአዕዋፋም ጭምር ነው ተብሎ ይታመናል፤ በዕለቱ ምግብ ከሰው አልፎ ለእንሳስት እና ለአዕዋፍም ይትረፈረፋል። ለከብቶችም የግጦሸ መሬት በየአካባቢው ይከለላል።
በተለያዩ አጋጣሚዎች የተጣሉ ታርቀው፣ የተራራቁ ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆች ተሰባስበው በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ ማድረግ የጋሞ ማስቃላ በዓል መገለጫ ነው።
መስከረም ወር የመጀመሪያው ቀን በጋሞ ዞን ”ሂንግጫ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ይህም አዲሱን ዓመት ለመቀበል ዝግጀት የሚደረግበት ቀን ነው። የተለያዩ አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ቀናትም ይገኛሉ።
ከገበያ ቀናቱ መካከል
• “ጋሜ ጊያ” የእርድ ከብቶች እና ለማስቃላ በዓል የሚሆኑ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ የሚገዛበት ነው፤
• “ዩሼ ጊያ” ወላድ እናቶች በማስቃላ በዓል ገበያ ወጥተው ዘና የሚሉበት ነው፤
• “ጎሻ ጊያ” የማስቃላ ዝግጅት ካበቃ በኋላ የመጨረሻው ገበያ ሆኖ እንደ ቅመማቅመም የመሳሰሉ ጥቃቅን ነገሮች የሚሸምቱበት እና ፈጥነው የሚመለሱበት በመሆኑ እንደወትሮው የደራ ገበያ አይሆንም።
ለ«ዮ…ማስቃላ» የሚደረጉት ዝግጅቶች ከተጠናቀቁ በኃላ ቀደም ሲል ለሶስት ወር ያህል ተከልሎ የቆየው የግጦሽ መሬት ለከብቶች ልቅ ይሆንና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በዓሉን ማክበር ይጀምራሉ።
በጋሞ ዞን የማስቃላ የእርድ ሥነ-ሥርዓት ከቦታ ቦታ ይለያያል። የመጀመሪያው በደመራው ዕለት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በማግሥቱ ይፈፀማል።
እርዱ በየቡድኑ በተደራጁ ቤተ-ዘመዶች ወይም ጎረቤቶች ገበያ ላይ አልያም አማካይ በሆነ ቦታ ይከናወናል።
ከቡድኑ አባላት ሴቶች ቦርዴ እና ማባያ ይዘው በእርዱ ቦታ ይገኛሉ።
ከየሥጋው ዓይነት የተመተረውን ተሰባስበው ከቀማመሱ እና በቦርዴ ካወራረዱ በኋላ የድርሻቸውን ሥጋ ተከፋፍለው ይለያያሉ። ወደ ቤት እንደደረሱም ቤተሰብ ተሰብስቦ ቁርጥ ሥጋ ይበላል።
ከሰዓት በኋላ ወይም ማታ ለሁሉም ቤተሰብ የሚበቃ ጎረድ ጎረድ በቅቤ ተለውሶ በትልቅ ወጭት ላይ ቀርቦ በባህላዊ ማንኪያ ይበላል።
በ2ኛው እና በ3ኛ ቀናት ጎድን ጥብስ በቂጣ ይበላል። ከሐረግ ቦዬ ብቻ የሚዘጋጅ ተሰርቶ ዮ...ዮ...ማስቃላ በመባባል ለሚመጡ ሰዎች ከባህላዊ መጠጥ ጋር ሣምንቱ እስኪያልቅ ድረስ ይቀርባል።
በባህሉ መሠረት ችቦ የሚወጣበት ሰዓት ሲደርስ አባት የራሱን ችቦ ለኩሶ የቅቤ ምንቸቱን፣ የቤቱን ምሰሶ፣ የከብቶቹን ጋጣ እና የበር ጉበኖችን ግራ እና ቀኝ በችቦው ጫፍ ያነካካል።
ከዚያም ወደ ውጪ ሲወጣ ወንድ ልጆች የየራሳቸውን ችቦ ተራ በተራ እየለኮሱ እና አባትን ተከትለው ዮ..ዮ..ማስቃላ እያሉ በመጨፈር ወደ ደመራው ቦታ ከደረሱ በኋላ አባት በቀዳሚነት ልጆች ደግሞ በተከታይነት ደመራውን ይለኩሳሉ።
በዕለቱ የሚዘጋጀው ባህላዊ ምግብ ገንፎ ሲሆን ይህንን ወንዶች ከጭፈራ ሲመለሱ ተሰባስበው ከአንድ ወጭት ዮ...ዮ ማስቃላ እያሉ ሁሉም የቤተሰብ አባላት፣ ዘመድ አዝማድ እና ጎረቤቶች ያለ ልዩነት በጋራ ይመገባሉ።
በጋሞ ብሔረሰብ የሚከበረው የማስቃላ በዓል በሶፌ ሥርዓት የታጀበ ነው።
የቀደመው ዓመት ማስቃላ በዓል ከተከበረ በኃላ የተጋቡ ሙሽሮች ከመስከረም አጋማሽ ጀምሮ ማምሻውን በአደባባይ ከመላው ህብረተሰብ ጋር የሚቀላቀሉበት እና ሁለቱም ተጋቢ ቤተሰቦች አንድ ላይ ሆነው ደስታቸውን የሚገልፁበት ሥርዓት ነው።
በዚህ ወቅት የሚወጡ ሙሽሮች በተለያዩ ባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጥ ተውበው ስለሚታዩ እንደቁንጅና ውድድር የተመልካችን ትኩረት ይስባል።
የመጨረሻው የማስቃላ ሽኝት በዓል ነው፤ ይህ ሥርዓት እንደየአባወራው አቅም በፈቀደ መጠን የሚፈፀም ነው። በዚህ ዕለት ሁሉም ያለ ፆታ ልዩነት በአደባባይ ላይ ወጥተው ያኑረን እስከ ወዲያኛው እንኖራለን እያሉ ይጨፍራሉ።
ከዚህ በኋላ ለመጪው ዓመት በሠላም በጤና ያድርሰን ተባብለው ፈጣሪን በመማፀን ዝግጅቱ ይቋጫል።
« ዮ ማስቃላ!»
Via ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ

ይህች ልጅ የምታለቅስበትን ምክንያት  ስትናገር እንዲህ ትላለች​"ስሜ ሰላም ይባላል፤ የምኖረው ጎንደር ውስጥ ነው። ልጅነቴ በአባቴ አጠገብ ሙሉ፤ በደስታና በብዙ ትልቅ ህልሞች የተሞላ ነበር....
18/08/2026

ይህች ልጅ የምታለቅስበትን ምክንያት ስትናገር እንዲህ ትላለች

​"ስሜ ሰላም ይባላል፤ የምኖረው ጎንደር ውስጥ ነው። ልጅነቴ በአባቴ አጠገብ ሙሉ፤ በደስታና በብዙ ትልቅ ህልሞች የተሞላ ነበር..."
​"አባቴ ትልቅ መደገፊያዬ ነበር፤ እኔን ለማስተማር፤ ትልቅ ደረጃ ደርሼ እንድኮራበት የማይፈነቅለው ድንጋይ አልነበረም።"

​"ነገር ግን ያ ሁሉ ደስታ በአንድ ጀምበር ፈረሰ... አባቴ በሞት ተለየኝ። እሱን ያጣሁበት ቀን የህይወቴ ብርሃን ሙሉ በሙሉ ጨለመ።"
​"ከእሱ ህልፈት በኋላ የህይወት ፈተና እርስ በእርሱ እየተደራረበ መጣብኝ፤ የሚያስተምረኝና ደግፎ የሚያቆመኝ ሰው አጣሁ።"
​"የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ የአባቴን አደራ ላለመጣል፤ ያንን ሁሉ ችግር ተሸክሜ ላለመውደቅ ሌት ተቀን ታገልኩ" ትላለች

​አባት ሲኖር መጠጊያ፣ ዋስትና እና የቤቱ ጠንካራ ምሰሶ ነው፤ እሱ ሲያልፍ ግን የመጠጊያው ጥላ አብሮ ይሸሻል

ሰላምን በቅርብ የሚታውቋት አፅናኗት አበረታቷት ደጋግ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሁኔታውን አመቻቹ ❤️

16/08/2026

Buju Star

1: ሁልጊዜ Busy ነኝ ማለት፤2: በትንሽ ነገር መበሳጨት/መናደድ፤3: ስለ ወደፊት እቅድ ማውራት አለመፈለግ፤4: ግጭትን/ጭቅጭቅን መሸሽ፤5: አጫጭር እና ደረቅ መልሶች ማብዛት፤
14/08/2026

1: ሁልጊዜ Busy ነኝ ማለት፤

2: በትንሽ ነገር መበሳጨት/መናደድ፤

3: ስለ ወደፊት እቅድ ማውራት አለመፈለግ፤

4: ግጭትን/ጭቅጭቅን መሸሽ፤

5: አጫጭር እና ደረቅ መልሶች ማብዛት፤

የአርባምንጭ - ኮንሶ - ጂንካ መንገድ ጥገና በትኩረት እየተከናወነ ነው ነሐሴ 07/2018 ዓ.ምአርባምንጭ፣  የአርባምንጭ - ኮንሶ - ጂንካ መንገድ ጥገና በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። ጥ...
13/08/2026

የአርባምንጭ - ኮንሶ - ጂንካ መንገድ ጥገና በትኩረት እየተከናወነ ነው

ነሐሴ 07/2018 ዓ.ም
አርባምንጭ፣

የአርባምንጭ - ኮንሶ - ጂንካ መንገድ ጥገና በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። ጥገናው የመንገዱን የአገልግሎት ደረጃ ከማሻሻሉም በላይ የተጠቃሚዎችን የጉዞ ጊዜ፣ ወጪ እና እንግልት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው።

የ235 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ፣ 211 ኪሎ ሜትር የድርብ አስፋልት ወለል ንጣፍ እና 24 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ያካተተ ነው። መንገዱ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል።

የመንገዱ የአገልግሎት ዘመን መጠናቀቅ፣ የትራፊክ ፍሰት መጨመር እና ተሽከርካሪዎች ከሕግ በላይ ጭነት መጫናቸው ለመንገዱ መበላሸት ዋና ምክንያቶች ናቸው። ይህም በትራንስፖርት እንቅስቃሴው እና በማኅበረሰቡ የዕለት ተዕለት ሕይወት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድሮ ቆይቷል።

ይህን ችግር ለመቅረፍ የሶዶ መንገድ አውታር አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት (ዲስትሪክት) በጣም የተጎዱ ክፍሎችን በመለየት፣ በተለያየ ደረጃ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

የጥገና ሥራው የአስፋልት መደረብ፣ የተቦረቦሩ ክፍሎችን በአስፋልት መሙላት፣ የመንገድ ትከሻ ማደስ፣ የጎርፍ ውሃ ማሳለጫ ቦዮችን ማጽዳት እና የተበላሹ ክፍሎችን መልሶ ማጠናከርን ያካተተ ነው። በተጨማሪም የዚሁ መንገድ አካል የሆነው የወዘቃ - ጋቶ የጠጠር መንገድ ሙሉ በሙሉ ተጠግኗል።

በአሁኑ ወቅት ከታቀደው 179 ኪሎ ሜትር የጥገና ሥራ ውስጥ 147 ኪሎ ሜትሩ በመጠናቀቁ የ82 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል። ከዚህ ውስጥ 129 ኪሎ ሜትሩ የአስፋልት፣ 18 ኪሎ ሜትሩ ደግሞ የጠጠር መንገድ ጥገና ነው።

መንገዱ በመጠገኑ በተጠቃሚዎች ላይ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። ከዚህ በፊት 6 ሰዓት ይፈጅ የነበረው ጉዞ በአሁኑ ወቅት ወደ 2 ሰዓት ዝቅ እንዲል አስችሏል። በተጨማሪም የትራንስፖርት ወጪ እና የአደጋ ሥጋት እንዲቀንስ አግዟል። ከዚህም ባለፈ የአሽከርካሪዎችን እንግልት፣ የተሽከርካሪ የጥገና እና የመለዋወጫ ወጪን ለመቀነስ ረድቷል።

ቅርንጫፍ ጽ/ት ቤቱ ቀሪዎቹን ውስን የጥገና ሥራዎች በቀጣይ ጥቂት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።

ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ሶስት ወጣቶች… ሶስት ህልሞች… ሶስት ቤተሰቦች የተሰበሩበት አሳዛኝ ክስተትከቤታቸው የወጡት እነዚህ ሶስት ወጣቶች እንደ ሌሎች ወጣቶች ህይወታቸውን ለመገንባት፣ ቤተሰባቸውን ለመርዳትና የተሻለ...
11/08/2026

ሶስት ወጣቶች… ሶስት ህልሞች… ሶስት ቤተሰቦች የተሰበሩበት አሳዛኝ ክስተት

ከቤታቸው የወጡት እነዚህ ሶስት ወጣቶች እንደ ሌሎች ወጣቶች ህይወታቸውን ለመገንባት፣ ቤተሰባቸውን ለመርዳትና የተሻለ ነገን ለማየት ህልም ነበራቸው። ዛሬ ግን እነዚያ ህልሞች በጥ ይት ተቀጩ።

በማህበራዊ ገጾች እየተሰራጨ ባለው መረጃ መሰረት፣ ሶስቱ ወጣቶች በህዝብ አውቶብስ ሲጓዙ ከመኪናው አስወርደው “ፋኖ ናችሁ” በሚል ጥርጣሬ ተገ ድለዋል።

ነገር ግን ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ነገር ፤ የሰው ልጅ ህይወት እንዴት ይህን ያህል ቀላል ሊሆን ቻለ?

እነዚህን ልጆች ለዘጠኝ ወር በማህፀናቸው የተሸከሙ እናቶች ነበሯቸው።
በድካም፣ በላብና በብዙ መስዋዕትነት ያሳደጓቸው አባቶች ነበሯቸው።
እህትና ወንድሞች፣ ጓደኞችና የሚወዷቸው ሰዎች ነበሯቸው።

ዛሬ ግን እነዚህ ቤተሰቦች ልጆቻቸውን ከፎቶ ብቻ እንዲያዩ ተደርገዋል። 💔

አንዲት እናት የልጇን የመጨረሻ ፎቶ ስትመለከት ምን ይሰማታል?
አንድ አባት በዓመታት የድካም ላቡን አፍስሶ ያሳደገውን ልጁን እንዲህ ሆኖ ሲመለከት ምን ይሰማዋል?
የልጃቸውን ድምፅ እንደገና መስማት ለማይችሉ ወላጆች የሚሰማቸውን ሀዘን የሚገልጽ ቃል ከየት ይገኛል? 😭

ሰው በማንነቱ፣ በጥርጣሬ ወይም በፖለቲካዊ ክስ ምክንያት ያለፍርድ ሊገደል አይገባም። የተጠረጠረ ሰው ካለ ህግ አለ፤ ምርመራ አለ፤ ፍርድ ቤት አለ።

ጥያቄያችን ፦ ህግ የት ነው? ፍትህስ የት ነው?

የሰው ህይወት ከማንኛውም ፖለቲካዊ አቋም በላይ ነው።
ግድያ ይቁም። ንፁሃን ከጥርጣሬ ይጠበቁ። ተጠያቂዎችም በህግ ፊት ይቅረቡ።

ለሶስቱ ወጣቶች ነፍስ እረፍትን፤
ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን፤
ለኢትዮጵያ ደግሞ ሰላምና ፍትህን እንመኝ። 🕯️🇪🇹

የእናት እንባ የሚያበቃበት፣ የአባት ልብ የሚረጋበት ቀን ይምጣ።
Via ዳኒ ታምራት

በራስ ቀለም!! Kako ❤️
10/08/2026

በራስ ቀለም!! Kako ❤️

መራራ እውነት ነው!በተላይም ሴቶች 🙌
10/08/2026

መራራ እውነት ነው!
በተላይም ሴቶች 🙌

09/08/2026

የአመቱ ምርጥ ንግግር🥰🥰🥰

Address

Arba Mintch

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when VisitArbaminch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share