28/01/2025
"......መጀመሪያ እራስሽን ውደጂው፣ ከዛ በኋላ ሰውን መውደድ ጀምሪ። ከዚያ አካባቢሽን ሀገርሽን በእራሱ ጊዜ ትወጃለሽ። ችግሩ የሰው ልጅ መጀመሪያ መውደድ የሚጀምረው ራሱን ሳይሆን ሌሎችን ነው። ከዚያ ባደገ ቁጥር ሰዎችን ጠልቶ ራሱን መውደድ ይጀምራል። ......እና እንዳልኩሽ አንድ ሰው ሀገር ከመግዛት እራሱን መግዛት ይከብደዋል፣ እራሱን የገዛ ሰው ግን አለምን መግዛት ይችላል። ስለዚህ እራስን መውደድ፣ መግዛት እና ማሸነፍ ከሁሉም ይቀድማል።....."
".......ሁሌም ከማንም እንደማታንሺ አስቢ፣ ለእራስሽ ክብር ስጪ፣ ራስሽን ውደጂ፣ ሁሉንም እችላለው ብለሽ ተነሺ፣ ፈተናዎችን በጥበብ እንደምትወጪ እመኚ፣ አንብቢ፣ ሁሌም ለነገሮች ዝግጂ ሁኚ፣ ያኔ ሁሉም ሰው ያከብርሻል። ሁሉንም ታሸንፊያለሽ፣ ሁሉም ይወድሻል። ሰነፍ አትሁኚ፣ የሰው ልጅ ውድቀት የሚጀምረው በስንፍናው ነው። ሰነፍ ሰው መጥፎ ነገሮሽን ሁሉ በጫንቃው ይሸከማል። ምክንያቱም በስንፍናው ስጋው የሚበላው ያጣልና። ሰው ሰነፍ ከሆነ የሰውን ይመኛል። ሌባ ይሆናል፣ ውሸትን ይናገራል፣ ነውርንም ይፈጽማል። ስለዚህ ብርቱ ሰው መሆን አለብሽ። አንቺ ማንንም መፍራት እና እንደዚህ ይሉኛል ማለት የለብሽም!! አንቺ በትክክል መልእክትሽን ካስተላለፍሽ ምን ችግር አለው ሰው የፈለገውን ቢል?? ሰውን አክብሪ!!!....."
ከ "ውብ" መጽሐፍ የተወሰደ
4ተኛ ዕትም በቅርብ ቀን!
ከጃዕፈር መጽሐፍ መደብር ያገኛሉ!