10/07/2023
የቅዱስ ጳወሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ላቦራቶሪ ዲፓርትመንት በISO እውቅና አገኘ፡፡
ይህን እውቅና ያገኘው በቅርቡ በተካሄደው 8ኛው ብሔራዊ የላቦራቶሪ ጉባዔ ላይ ነው፡፡ ላቦራቶሪው በጠቅላላላው በቁጥር 13 ቴስቶች እውቅና አግኝቷል፡፡ ይህ ማለት በማይክሮባዮሎጂ አንድ እና አስራ ሁለት ደግሞ በክሊኒካል ኬሜስትሪ ቴስቶች ነው፡፡
የቅዱስ ጰውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ማህበረሰብ መላውን የላቦራቶሪ ሰራተኞች /ባለሙያዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እንወዳለን፡፡