Tesfa

Tesfa የሰው ልጆችን በእውነተኛ ተስፋቸው ላይ እንዲያተኩሩ ለመርዳት የተከፈተ ገፅ ነው

እግዚአብሔር ለእኛ ለሕዝቡ የሰጠን ትእዛዝ የምንኖርባትን  ምድር ሰላም እንድንፈልግ  እና ስለ ምድራችንም እንድንጸልይ   ነው። ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን እና ለመሪዎቻችን መጸለይ አለብን። መሪ...
02/06/2026

እግዚአብሔር ለእኛ ለሕዝቡ የሰጠን ትእዛዝ የምንኖርባትን ምድር ሰላም እንድንፈልግ እና ስለ ምድራችንም እንድንጸልይ ነው። ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን እና ለመሪዎቻችን መጸለይ አለብን።
መሪዎች በጥበብ እንዲመሩ፣ ፍትሕ እንዲሰፍን፣ ሕዝብም በአንድነት እንዲኖር መጸለይ። ለሀገራችን የሚያስፈልጋት የእግዚአብሔር ሰላም ነውና።

ኤርምያስ 29:7 በእርስዋ ሰላም ሰላም ይሆንላችኋልና ወደ እርስዋ ላስማርክኋችሁ ከተማ ሰላምን ፈልጉ፥ ስለ እርስዋም ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ።

ሀገር ሰላምን፣ ሕዝብም ፈውስን ይሻል።ይህ የሚሆነው ደግሞ በጸሎት፣ በትሕትና እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ነው።በዚህ ዘመን ሀገራችን ሰላምን፣ ፈውስን እና የእግዚአብሔርን ምሕረት እጅግ ት...
01/06/2026

ሀገር ሰላምን፣ ሕዝብም ፈውስን ይሻል።
ይህ የሚሆነው ደግሞ በጸሎት፣ በትሕትና እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ነው።
በዚህ ዘመን ሀገራችን ሰላምን፣ ፈውስን እና የእግዚአብሔርን ምሕረት እጅግ ትሻለች። እንደ ሀገር ለምናቅደው ነገሮች ሁሉ፣ ተስፋችን እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ብንጮህ፣ እርሱ ይሰማናል። የተሰበረ ልባችንንም ይፈውሳል፣ ለሀገራችንም ሰላሙን ያመጣልናል።

2 ዜና 7:14 በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢልፈጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።


Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

እግዚአብሔር የልጆቹን ጩኸት ይሰማል። አንዳንድ ጊዜ በችግር፣ በሀዘን ወይም በጭንቀት ውስጥ ልታልፍ ትችላለህ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ጸሎትህን  ይሰማል፣ የምታልፍበትንም ያውቃል፤ ደርሶም  ...
31/05/2026

እግዚአብሔር የልጆቹን ጩኸት ይሰማል። አንዳንድ ጊዜ በችግር፣ በሀዘን ወይም በጭንቀት ውስጥ ልታልፍ ትችላለህ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ጸሎትህን ይሰማል፣ የምታልፍበትንም ያውቃል፤ ደርሶም በጊዜው ይረዳሀል።
እግዚአብሔር ቅርብ ነው፣ የሚሰማ እና የሚያድንም አምላክ ነው።
ዛሬ በጭንቀት ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ጩኸትህን ይሰማል፤ በጊዜውም ይደርስልሀል።

“ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።”— መዝሙር 34፥17

እውነተኛ እረፍትና እፎይታ የሚገኘው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ  ብቻ ነው።በሀጢያት ወይም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ደክመሀል? ኢየሱስ ወደ እኔ ና፤ እረፍት እሰጥሃለሁ ብሎ ይጠራሀል።እ...
28/05/2026

እውነተኛ እረፍትና እፎይታ የሚገኘው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
በሀጢያት ወይም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ደክመሀል? ኢየሱስ ወደ እኔ ና፤ እረፍት እሰጥሃለሁ ብሎ ይጠራሀል።
እርሱ የሚሰጠው እረፍት: ከሀጢዓተኝነት እና ከበድለኝነት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ ከጭንቀትና ከፍርሃት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ በልብ ውስጥ የተረጋጋ ሰላምና እፎይታ የሚሰጥ እረፍት፣ የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት እውነተኛ እረፍት ነው።
ዛሬ ወደዚህ እረፍት ተጠርተሀል!

ማቴዎስ 11:28 እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።

እግዚአብሔር በማንኛውም የሕይወት ሁኔታ ውስጥ ለልጆቹ ቅርብ ነው። ከአደጋ ምትሸበት እና የምትጠለልበት መጠጊያ ቦታ ነው። እግዚአብሔር በድካምህ ጊዜ የሚያበረታህ ኃይልህ ነው። አንዳንድ ጊዜ ...
27/05/2026

እግዚአብሔር በማንኛውም የሕይወት ሁኔታ ውስጥ ለልጆቹ ቅርብ ነው። ከአደጋ ምትሸበት እና የምትጠለልበት መጠጊያ ቦታ ነው። እግዚአብሔር በድካምህ ጊዜ የሚያበረታህ ኃይልህ ነው። አንዳንድ ጊዜ በሕይወትህ የምታልፍበት ነገር ከአቅምህ በላይ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በዚያ ጊዜ ውስጥ እንኳ የሚያጸናህ እና እንድትቀጥል የሚያደርግ ኃይል ይሰጥሀል። እግዚአብሔር አምላክ በችግርህ ጊዜ ከአንተ ጋር ያለ፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና እና ተስፋ የሚሰጥ አባት ነው።

ዛሬ በሕይወትህ ውስጥ ድካም፣ ፍርሃት ወይም ጭንቀት ካለ፣ ብቻህን አይደለህም። እግዚአብሔር መጠጊያህ፣ ኃይልህ እና ረዳትህ ነው። ወደ እርሱ በጸሎት ብትቀርብ ሰላሙን ይሰጥሃል፣ ልብህንም ያበረታል።

መዝሙር 46:1 አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።

በዚህ ቃል መሰረት ፈተና ወይም ፍርሃት ቢኖር እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን ይነግርሀል። ብቻህን አይደለህም፤ እርሱ ይመራህል፣ ያጽናናሀል፣ ኃይልም ይሰጥሀል።በምታልፍበት ሁኔታ ሳይሆን በእ...
26/05/2026

በዚህ ቃል መሰረት ፈተና ወይም ፍርሃት ቢኖር እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን ይነግርሀል። ብቻህን አይደለህም፤ እርሱ ይመራህል፣ ያጽናናሀል፣ ኃይልም ይሰጥሀል።
በምታልፍበት ሁኔታ ሳይሆን በእግዚአብሔር ህልውና ታመን። እርሱ በምትሄድበት ሁሉ ከአንተ ይሆናል። ፍርሃትህን አስወግደህ፤ በእግዚአብሔር ብቻ ታምነህ ምትኖርበትን ህይወት ዛሬ ወስን!

"በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?” ኢያሱ 1፥9

እግዚአብሔር በሰው ህይወት ውስጥ የሚፈቅደውን ሁሉ ነገር ለበጎ ይለውጠዋል።  ዛሬ የምታልፍበትን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይቀይረዋል።አንዳንድ ጊዜ የምታልፍበት ነገር ለምን እንደሚሆን ላይገባህ...
15/05/2026

እግዚአብሔር በሰው ህይወት ውስጥ የሚፈቅደውን ሁሉ ነገር ለበጎ ይለውጠዋል። ዛሬ የምታልፍበትን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይቀይረዋል።

አንዳንድ ጊዜ የምታልፍበት ነገር ለምን እንደሚሆን ላይገባህ ይችላል፤ ህመም፣ መዘግየት፣ ችግር ወይም ውድቀት ቢኖርም በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እግዚአብሔር እየሠራ ነው።
እርሱ ከባድ ነገሮችን እንኳ ለመልካም ያደርጋቸዋል።
ዛሬ ያልገባህ ሁኔታ ቢኖርም ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ከህይወትህ አንድም ክፍል አይለይም። እርሱ እያንዳንዱን ነገር ለመልካም ፍጻሜ እያዘጋጀህ ነው።

ሮሜ 8:28 እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።

በጣም ከባድ ጊዜያቶችን በምታሳልፍበት ጊዜ እንኳን  እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው። ዳዊት  ብዙ ጦርነት፣ ፍርሃት እና አደጋ አጋጥሞት ነበር፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር አብሮነት ላይ ሙሉ በሙ...
14/05/2026

በጣም ከባድ ጊዜያቶችን በምታሳልፍበት ጊዜ እንኳን እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው። ዳዊት ብዙ ጦርነት፣ ፍርሃት እና አደጋ አጋጥሞት ነበር፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር አብሮነት ላይ ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ ባለ ጊዜ እንኳ እንደማይተወው ስለሚያውቅ ነው።

ዛሬ ምንም አይነት ጭንቀት ቢገጥምህ፣ ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው፣ እርሱም ሰላምን ይሰጥሃል።

መዝሙር 23:4 በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ፡ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።

የእስራኤል ሕዝብ በመከራና በስደት ውስጥ ባሉበት ጊዜ እግዚአብሔር ግን ለእነርሱ ያለውን  ፍቅር እና መልካም ዕቅድ ነግሯቸዋል። እነርሱ ተስፋ ቢቆርጡም እግዚአብሔር ግን እኔ ስለእናንተ መልካ...
13/05/2026

የእስራኤል ሕዝብ በመከራና በስደት ውስጥ ባሉበት ጊዜ እግዚአብሔር ግን ለእነርሱ ያለውን ፍቅር እና መልካም ዕቅድ ነግሯቸዋል።
እነርሱ ተስፋ ቢቆርጡም እግዚአብሔር ግን እኔ ስለእናንተ መልካም አሳብ አለኝ ብሎ ተስፋን እንደሰጣቸው፤ ይህ ቃል ዛሬም ለአንተ ህይወት ይሰራል፡፡ ለህይወትህም ትልቅ መጽናናት ነው።
አንዳንድ ጊዜ ሕይወት ግራ ሊያጋባህ ይችላል፤ ፈተና፣ መዘግየት ወይም ያልተጠበቀ ነገር ሲመጣ እግዚአብሔር እንደረሳህ እና እንደተወህ ሊሰማን ይችላል።
ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው አሳብ የሰላም፣ የተስፋ እና የመልካም ፍጻሜ ነው።
እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው የመጨረሻው ታሪክህም በእርሱ በእጁ ነው።

ዛሬ በምንም ዓይነት ግራ መጋባት እና በጭንቀት ብታልፍ፣ እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው ዕቅድ መልካም መሆኑን አስታውስ። እርሱ ተስፋ የሚሰጥ አምላክ ነው፤ ወደፊትህም በእጁ ውስጥ ነው።

ኤርምያስ 29:11 ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።

ሕይወት ብዙውን ጊዜ የፍርሃት፣ የጥርጣሬ እና የድክመት ጊዜያትን እንድታልፍ ታስገድድሀለች።  ነገር  ግን ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው።የእግዚአብሔር መገኘት ከሚገጥምህ ...
12/05/2026

ሕይወት ብዙውን ጊዜ የፍርሃት፣ የጥርጣሬ እና የድክመት ጊዜያትን እንድታልፍ ታስገድድሀለች። ነገር ግን ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው።
የእግዚአብሔር መገኘት ከሚገጥምህ ከማንኛውም ችግር ይበልጣል።

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 41:10

Address

Addis Ababa

Telephone

+251912251111

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tesfa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Tesfa:

Share

Category