25/02/2017
sarah abebe ሰለ ድንግል ማርያም ሰለ መልአክት ሰለ ፃድቃናት አማላጅነታቸዉ
ማስረጃ፡ሰለ እመቤታችን ቅድስናዋ፡ክብሯ፡ድንግልናዋና አማላጅነቷ፡ መዝ 9:11 መዝ
13:10 መዝ 44:9 መዝ 131:13 መዝ 86:5 መዝ 44:2 ኢሳ 7:14
ኢሳ49:23ኢሳ60:14 (2)ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም ዘፍ
3:221ኛ ሳሙ16:1 ኢሳ9:6 ዳን7:14 ሆሴ13:4 ዘካ 9:9-10 ሚክ5:2 ሉቃ1:32-33
ዮሐ10:30 ሉቃ2:12 ዮሐ14:7 ሮሜ9:5 (3ኛ) ጸድቃን ሰማዕታት ያማልዳሉ ዘፍ
18:17-18 ዘፍ18:23:24 ዘፍ20:7 ዘፍ33:3 ዘፍ42:6 1ኛ ሳሙ28:14 2ኛ ሳሙ1:2
ነገ4:9 2ኛ ነገ4:32-35 መዝ88:34 ማቴ18:18 ዮሐ20:23ይነበብ Like · Report ·
Yesterday at 2:28pm Esrsh Ladder Man በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር
ዘምሩ፥ በአሕዛብም መካከል አደራረጉን ንገሩ፤ መዝሙረ ዳዊት 9 : 11 እሺ ትክክል ነው
ለእግዚአብሔር ዘምሩ ነው የሚለው እንጂ ድንግል አማላጅ ነች አይልም፡፡ አንድ ነገር
ልንገርሽ አንድ ሠው በምድር እሥካለ ድረሥ አዎ እኛም እናማልዳለን እንግዲህ
እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር
ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5 : 20 ነገር ግንአንድ
ሠው ከሞተ በሁዋላ ምልጃው ያበቃል እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት
የሆኑት ብዙ ናቸው፤ ወደ ዕብራውያን 7 : 23 ሕያዋን እንዲሞቱ ያውቃሉና፤ ሙታን ግን
አንዳች አያውቁም፤ መታሰቢያቸውም ተረስቶአልና ከዚያ በኋላ ዋጋ የላቸውም።
ፍቅራቸውና ጥላቸው ቅንዓታቸውም በአንድነት ጠፍቶአል፥ ከፀሐይ በታችም በሚሠራው
ነገር ለዘላለም እድል ፈንታ ከእንግዲህ ወዲህ የላቸውም። መጽሐፈ መክብብ 9 : 4-6 ,
ክርስቶስ ኢየሱስ ግን ሞትን ድል አድርጎ ስለተነሳ ዘለአለም ካህን ነው፡፡ እስኪ ልጠይቅሽ
አሁንም አማላጅ የሚያስፈልግ ከሆነ ኢየሱስ ለምን መጣ? ማለቴ ልክ እንደ ብሉይ ኪዳኑ
አይነት ምልጃ,,,,,,,ለምን እንደ ብሉይ ኪዳን አንቀጥልም ነበር????????????? ሰለ
ድንግል ሰለ መልአክት ሰለ ፃድቃናት አማላጅነታቸዉ ማስረጃ ብዙ ጥቅሥ ልከሽልኛል
ግን ሁሉም በምድር ላይ ሳሉ የሠሩት ምልጃ ነው በምድር እስካለን እንኳን እነሱና እኛም
እናማልዳለን ነገር ግን ሙታን ከፀሐይ በታችም በሚሠራው ነገር ለዘላለም እድል ፈንታ
ከእንግዲህ ወዲህ የላቸውም። መጽሐፈ መክብብ 9 : 4-6 ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ
ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም ብለሽ የላክሽልኝ ጥቅሶች ደግሞ ሁሉም የጌታችንና
መደሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነትና አምላክነት የሚናገሩ ናቸው እንጂ አማላጅ
አይደለም አይሉም ደግሞ አማላጅ አይደለም የሚል ከሆነ ሌላ ጋር ደግሞ የሞተው፥
ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው
ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 8:34) ........... (ወደ ዕብራውያን ምዕ. 7)
---------- 23፤ እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤
24፤ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤ 25፤ ስለ እነርሱም
ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር
የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። (1ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕ. 2) ----------
1፤ ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ
ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 2፤ እርሱም
የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ
ኃጢአት እንጂ። 3፤ ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን። 4፤
አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ
የለም። (የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 22) ---------- 31፤ ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥
ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ 32፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ
አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ። (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች
ምዕ. 5) ---------- 19፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ
ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። 20፤
እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤
ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን። 21፤ እኛ በእርሱ ሆነን
የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት
አደረገው። አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው
መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ 1ኛ ወደ
ጢሞቴዎስ 2 : 5 ይላል እና እግዚአብሔር ይዋሻል? መፀሀፍ ቅዱስ እርስ በርሱ
ይጋጫል?????????????? የላክሽልኝን ጥቅሶች በደንብ አንብቢያቸው ጌታ
ይባርክሽ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!