Zekr Menzuma & Neshida

Zekr Menzuma & Neshida የቀደምት ታላላቅ ዑለማዎቻችንን እና በህይወት ያሉትን ዑለማ

እናንተ እዚህ ኢምራን እፎይ እያላችሁ ታወራላችሁ ይህች እህታችን ግን መላዉን ዓለም እያስጨነቀች ነዉ ቲክታክን ተቆጣጥራዋለች ክርስsትናን ብትንትኑን አዉጥታዋለች 💪 ብቻዋን ሆና 20 እየገጠመ...
24/05/2026

እናንተ እዚህ ኢምራን እፎይ እያላችሁ ታወራላችሁ ይህች እህታችን ግን መላዉን ዓለም እያስጨነቀች ነዉ ቲክታክን ተቆጣጥራዋለች ክርስsትናን ብትንትኑን አዉጥታዋለች 💪 ብቻዋን ሆና 20 እየገጠመች ትዘርራቸዋለች ... ዓለም በሙሉ ወደ እስልምና እየተቀየረ ነዉ !! ፎሎ አድርጓት https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96bn5qXQu2i

11/04/2026

አክሱም በስራችሁ እፈሩ❗️እጅግ አሳፋሪ ስራ ነው❗️ ሰው ተወልዶ ባደገበት ሀገር ሀይማኖቱ ሙስሊም ስለሆነ ብቻ የሚያገልሉ ሰዎች በዚህ በስልጣኔ ዘመን ኖረው ማየቱ በራሱ ያስገርማል❗️
https://t.me/ZEKR_MENZUMA

አክሱም በስራችሁ እፈሩ! እጅግ አሳፋሪ ስራ ነው ቱ! ሰው ተወልዶ ባደገበት ሀገር ሀይማኖቱ ሙስሊም ስለሆነ ብቻ የሚያገልሉ ሰዎች በዚህ በስልጣኔ ዘመን ኖረው ማየቱ በራሱ ያስገርማል!
11/04/2026

አክሱም በስራችሁ እፈሩ! እጅግ አሳፋሪ ስራ ነው ቱ! ሰው ተወልዶ ባደገበት ሀገር ሀይማኖቱ ሙስሊም ስለሆነ ብቻ የሚያገልሉ ሰዎች በዚህ በስልጣኔ ዘመን ኖረው ማየቱ በራሱ ያስገርማል!

ሃስቡንአላሁ ተአላ ወኒእመልወኪል በ አክሱም ከተማ እህት ወንድሞቻችን ላይ እየደረሰ ያለ ግፍ ከ ቀን ወደቀን እየጨመረ መቶል አብረዋቸው ለኖሩ ሂወታቸውን ለ አገራቸው መስዋት ላደረጉ ያልሆኑ ...
11/04/2026

ሃስቡንአላሁ ተአላ ወኒእመልወኪል
በ አክሱም ከተማ እህት ወንድሞቻችን ላይ እየደረሰ ያለ ግፍ ከ ቀን ወደቀን እየጨመረ መቶል አብረዋቸው ለኖሩ ሂወታቸውን ለ አገራቸው መስዋት ላደረጉ ያልሆኑ ለማንም አይሆኑም እዛ ያለው ሀላፊነት ላይ የተቀመጠው ለ ግል ፖለቲካው እህት ወንድሞቻችን ላይ እያደረሰ ያለው ግፈ በደል ተወልደው ባደጉበት አገረ የመብት ገፈፋ እጅግ በጣም የሚያምና የማንረሳው ነው!
የ እኩል መብታቸው እየተገፈፈ ነው ይህ መብቃት አለበት

መስጅድ ውስጥ የፀጥታ አካላት  ከነጫማቸው  በመግባት ቁርዓንን መቅደዳቸው ተገለፀዛሬ በአክሱም ከተማ የጸጥታ አካላት የጁማዓ ሰላት አትሰግዱም በሚል ሙስሊሞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው የአይን ...
11/04/2026

መስጅድ ውስጥ የፀጥታ አካላት ከነጫማቸው በመግባት ቁርዓንን መቅደዳቸው ተገለፀ

ዛሬ በአክሱም ከተማ የጸጥታ አካላት የጁማዓ ሰላት አትሰግዱም በሚል ሙስሊሞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው የአይን አማኞች ተናግረዋል

ከዚህ በተጨማሪም የፀጥታ አካላት ከነጫማቸው መስጂድ ውስጥ በመግባት ቁርአንን በመቅደድ መስጂዱን እንደተዳፈሩ ተገልጿል።

​በዛሬው ዕለት በአክሱም ከተማ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ እጅግ አሳዛኝ እና ታሪክ የማይረሳው አኩይ ድርጊት በሙስሊም ማህበረሰብ ደርሷል።

ይህ ድርጊት አዲስ እንዳልሆነና ለብዙ ዓመታት በአክሱም ከተማ ሙስሊም ነዋሪዎች ላይ ሲደርስ የቆየው የሃይማኖት ጭቆና እና በደል አካል አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጠቁሟል።

ዛሬ ከጁማዓ ሰላት በፊትና በኋላ የከተማዋ የጸጥታ ምክትል ኃላፊ ተክድሮስ ሸዋ የሚባሉ ግለሰብ ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ማን ፈቀደላችሁ በሚል ለጁምዓ ሰላት ዝግጅት ይውሉ የነበሩ ሁለት ስፒከሮችን እና ሸራዎችን መውስዳቸውን መረጃ ያመለክታል ።

ምዕመናኑ የጁምዓ ሰላትን አጠናቅቀው ስፒከሮቻቸው እንዲመለሱላቸው እና የመስገድ መብታቸው እንዲከበር ጥያቄ ቢያቀርቡም ቀደም ብለው በተዘጋጁ የጥፋት ሀይሎች ከአራት አቅጣጫ ድንጋይ እንደተወረወረባቸው የመረጃ ምንጫችን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ዩኒፎርም የለበሱ እና ሲቪል የጸጥታ አካላት በሰላማዊው ምዕመን ላይ ድብደባ የፈጸሙ ሲሆን በዚህም ምክንያት ስምንት ያህል ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱና በርካታ ወንድሞችም መታሰራቸው ተገልጿል።

የጥፋት ሀይሎች ያደረሱት ጥቃትና እንግልት አልበቃ ብሏቸው የሙስሊሙን ማህበረሰብ መስጂዶች እና የንግድ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ሲያደርጉ እንደነበር መረጃ የሳያል።

https://t.me/ZEKR_MENZUMA

● Them:- እስራኤል ጀግና ናት፣ የኢራኑን መሪ ገደለችው። ● Me:- ምነው የእናንተን አምላክ እንኳ ገድላ የለም እንዴ !😂https://t.me/ZEKR_MENZUMA
01/03/2026

● Them:- እስራኤል ጀግና ናት፣ የኢራኑን መሪ ገደለችው።

● Me:- ምነው የእናንተን አምላክ እንኳ ገድላ የለም እንዴ !😂

https://t.me/ZEKR_MENZUMA

መልከ ጥፉውና 350 ኪታቦችን የፃፈው አቡ ዑስማን አልጃሒዝ እንዲህ ሲል ቂሳውን ያወጋናልበአንዲት ሴት እንጂ በማንም አላፈርኩም።አንድ ጊዜ አንዲት ቆንጅዬ ሴት ቤቴ ደጃፍ መጣች። ፈገግ አልኩ...
15/01/2026

መልከ ጥፉውና 350 ኪታቦችን የፃፈው አቡ ዑስማን አልጃሒዝ እንዲህ ሲል ቂሳውን ያወጋናል

በአንዲት ሴት እንጂ በማንም አላፈርኩም።
አንድ ጊዜ አንዲት ቆንጅዬ ሴት ቤቴ ደጃፍ መጣች። ፈገግ አልኩላት። እሷም
"እፈልግሀለው" አለችኝ
"ምነው በሰላም ነው?" አልኳት
"ተከተለኝ" ብላኝ ሄደች። ተከትያት ሄድኩ።
የጌጣጌጥ ሰራተኛ ዘንድ ወሰደችኝና
"የሱ አይነት" ብላው ሄደች
ግራ ስለገባኝ "ምንድነው?" ስለው
"ቀለበቷ ላይ የሸይጣን ሱራ እንድሰራላት ጠየቀችኝ እኔም 'ሸይጧንን የት አውቄው?' አልኳት አንተን ይዛ መጣችና ይኸው የሱ አይነት ብላኝ ሄደች።"

አይገርምም የራሱን የአስቀያሚነት ጥግ ሳይደብቅ በኪታቡ ላይ ማስፈሩ?

የሚገርመው የሞተው ቤቱ ውስጥ ታሞ በተኛበት የተከማቹ በርካታ ኪታቦች ተደርምሰውበት ነው።

በኪታብ ኖረ በኪታብ ሞተ

https://t.me/ZEKR_MENZUMA

ሚስት ባሏ እንግዳ ይዞ እየመጣ ስልችት ብሏት ስሞታ ለማቅረብ ወደ ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) መጣች ችግሯ ዘርዘር ኣድርጋ  ነገረቻቸው ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) ዝም ብለው ሰምተዋት ምንም ኣልመለሱላትም ሴትዮዋ...
29/12/2025

ሚስት ባሏ እንግዳ ይዞ እየመጣ ስልችት ብሏት ስሞታ ለማቅረብ ወደ ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) መጣች ችግሯ ዘርዘር ኣድርጋ ነገረቻቸው ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) ዝም ብለው ሰምተዋት ምንም ኣልመለሱላትም ሴትዮዋ ከሄደች በኋላ ለባሏ ኣስጠርተው ዛሬ ኣንተ ቤት እንግዳ ነኝ ኣሉት ባል በጣም ተደስቶ ለሚስት ነገራት ሚስትም በጣም ተደሰተች ራሕመተል ዓለም እቤቷ ሊገቡ ነዋ ቤት ያፈራው ነገር በደስታ ኣዘጋጀች ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) ገብተው ከተስተናገዱ በኋላ ለባልየው ስወጣ ሚስትህ እኔ በምወጣበት በር ወደዛ እንድትመለከት ንገራት ኣሉት
ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) ሲወጡ ሚስት ትመለከታለች ከኋላቸው ጊንጥ እንሽላሊት ሌላም ጎጂ ነፍሳቶች ተከትሏቸው ሲወጡ ኣየች ሚስት ደንግጣ ዞረባት ከዚያም ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) ኣሉ "ኣንድ እንግዳ ከተጠራበት ቤት ሲወጣ ልክ እንደዚህ ከዛ ቤት ችግር በላ እና ጎጂ ነፍሳቶች ተከትለዉት ይወጣሉ"

እንግዳ የሚበዛበት ቤት ኣላህ የሚወደው ቤት ነው

ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ ይላሉ ኣላህ ኸይር የፈለገለት ሰው ስጦታ ይልክለታል ያስጦታ ምንድን ነው ተብለው ሲጠየቁ እንግዳ ሲገባ ሪዝቅ ይዞ ሲወጣ የቤቱን ወንጀል ጠርጎ የሚሄድ

"እንግዳ የማይገባበት ቤት መላኢካ ኣይገባበትም"ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ)
"እንግዳ ወደ ጀነት ኣመላካች ነው" ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ)
"በኣላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር"

እንግዳ መጋበዝ ኣለብኝ ብለን የግድ ከኣቅማችን በላይ መጣጣር የለብንም ቤት ባፈራው ሊላህ ብለን ብቻ እንግዳውን ቀልቡ ለማስደሰት በኢኽላስ ከሆነ እንግዳው የሚያስደስተው የምግቡ ኣይነት ሳይሆን እሱን ኣክብረን መጥራታችን ነው!
ኣላህ እንግዳን የምናከብርበት ተውፊቅ አላህ ይስጠን.....🤲

https://t.me/ZEKR_MENZUMA

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑንየሁላችንም አባት የነበሩት የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ አኼራ ሄደዋል::የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ...
19/10/2025

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

የሁላችንም አባት የነበሩት የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ አኼራ ሄደዋል::

የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ አኼራ ሄደዋል::

ህልፈታቸው የመላው ሀገራችን ህዝብ ሀዘን ነው:: እኚህን ታላቅ አባት ላበርክቷቸው በሚመጥን መልኩ ስርዓተ ቀብራቸው በመንግስት ደረጃ ኢስላማዊ ስነ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ መፈፀም ይኖርበታል::

ሀገራችን ታላቅ አባት አጥታለች:: ሀዘናችን መሪር ቢሆንም የአላህን ውሳኔ ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለም::

አላህ መልካም አበርክቷቸውን ይቀበላቸው፣ ምህረቱን ይለግሳቸው፣ በጀነተል ፊርዶስ ይመንዳቸው

አጭር ናት ግን ትልቅ 🗨️መልእክት❗️
10/10/2025

አጭር ናት ግን ትልቅ 🗨️መልእክት❗️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zekr Menzuma & Neshida posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Establishment

Send a message to Zekr Menzuma & Neshida:

Share