Nur Broadcast

Nur Broadcast Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nur Broadcast, P. O. Box 1696, Kella.

03/04/2026

jechuun tawhiidaan Rabbiif harka kennu, ajajamuun Isaaf masakamuu, shirkii fi warra shirkii hojjatan irraa qulqullaa’udha.”

“tawhiidaan Rabbiif harka kennu” jechuun gabrichi Rabbiin tokkichoomsu fi Isa qofa gabbaruun Isaaf harka kennu. “ajajamuun Isaaf masakamuu” jechuun wanta Rabbiin ajajee hojjachuu fi wanta Inni dhoowwe dhiisu. “shirkii fi warra shirkii hojjatan irraa qulqullaa’u.” Jechuun shirkii irraa bilisa ta’uu fi fagaachu. Shirkii irraa qulqullaa’un warra shirkii hojjatan irraayis akka qulqullaa’an barbaachisa.[7]
Islaamni utubaalee (arkaana) shan qaba. Isaaniis:

Laa ilaah ill-Allah Muhammadan rasulullah (Dhugaan gabbaramaan Rabbiin malee hin jiru, Muhammad Ergamaa Rabbiiti)” jedhenii ragaa bahuu.

Salaata sirnaan salaatu

Zakaa kennu

Ji’a ramadaanaa soomu

Namni hajju danda’u hajjii hajjuu
Amboti Bro

02/04/2026

☪️ #ጉዞ ወደ #ኢስላም አላሁ አክበር 😘 ሰዎች ወደ ኢስላም #እንደጎረፉ ነው ማሻአላህ

አላህ የሚደውን ይመራል ማሻአላህ 😘👐😍😍😍

Kantiibaan magaalaa New York Zahran Mamdani, Muslima, poolisoota Muslimaa waliin osoo sooma isaanii hin furin dura yaroo...
18/03/2026

Kantiibaan magaalaa New York Zahran Mamdani, Muslima, poolisoota Muslimaa waliin osoo sooma isaanii hin furin dura yaroo rabbiin kadhatan.

Mul'ata kanaan dura hin argamne kan ergaa cimaa qabu: Islaamummaan qaama hawaasa Ameerikaa sochii fi dhiibbaa guddaa qabu ta'eera.

Yaa Rabbii Islaamaa fi Muslimootaaf ulfina kenni, injifannoo isaaniif kenni, bakka hundatti humna isaaniif kenni.

16/03/2026

Look it.

ኢየሱስ ጌታ ነው የምል ትውልድ ሙሉ በሙሉ መንግስተ ሰመይ አይገበም።ክርስቲያኖች ፍፅሞ መንግስተ ሰመያት አይገቡም። እየሱስ ክርስቶስ ነው የተናገረው።
06/03/2026

ኢየሱስ ጌታ ነው የምል ትውልድ ሙሉ በሙሉ መንግስተ ሰመይ አይገበም።
ክርስቲያኖች ፍፅሞ መንግስተ ሰመያት አይገቡም። እየሱስ ክርስቶስ ነው የተናገረው።

06/03/2026

ትት! ወሃቢያ!፦ ውሸትን እውነት የማስመሰል የፕሮፓጋንዳ ወጥመድ
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

በአሕመዲን ጀበል
✅✅✅✅✅✅
መልዕክቱ በስፋት እንዲዳረስ በሁሉም መንገድ ሼር ያድርጉ።
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶

በኢትዮጵያ ዲጂታል ምኅዳር የሚታዩት 'ወሃቢያ'፣ 'አክራሪ' እና 'አሸባሪ' የሚሉ የጅምላ ፍረጃዎች ተራ የስድብ ቃላት ሳይሆኑ፤ በጥናት ላይ የተመሠረቱና አእምሮን ለመቆጣጠር የታለሙ የሥነ-ልቦና ጦርነት መሣሪያዎች ናቸው። ይህ ስልታዊ አካሄድ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ሕጋዊ የመብት ጥያቄዎችና የታሪክ ባለቤትነት ፍለጋን በማጠልሸት፣ ማህበረሰቡን በሀገር ግንባታ ውስጥ ተገፊና ድምፅ አልባ (Marginalized) ለማድረግ በብዙ አጋጣሚዎች በስፋት የሚታይ የተቀነባበረ ስልት ነው።

እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባው እውነት፦ ይህ ትንታኔ በሃይማኖቶች መካከል ያለን ነፃ የሐሳብ ልዩነት ወይም ትምህርታዊ ክርክር የሚቃወም አይደለም። ይልቁንም ትኩረቱ ቃላት ከመንፈሳዊ ይዘታቸው ተነጥለው እንደ ፖለቲካዊ የማጥቆሪያ ታርጋ ለሥነ-ልቦና ጦርነት ጥቅም ላይ በሚውሉበት አደገኛ አካሄድ ላይ ነው። የዚህ ስልታዊ ዘመቻ ዋና ዋና ግቦች የሚከተሉት ናቸው፦

1. አመክንዮአዊ ሽባነትን መፍጠር
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
ማህበረሰቡ የቀረበለትን መረጃ በምክንያት ከመመርመሩ በፊት፣ በውስጡ ስር የሰደደ 'የህልውና ስጋት' እና ፍርሃት እንዲነግሥ በማድረግ የማሰብ አቅሙን ማደንዘዝ። በዚህ ስልት፣ የፕሮፓጋንዳው ሰለባ የሆነ ሰው ከእውነት ይልቅ ለስሜታዊ ትረካዎች ተገዥ እንዲሆን ይደረጋል።

2. ጥቃትን ማጽደቅና ማኅበራዊ ፈቃድ ማውጣት፦
♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦
ተጠቂውን አካል 'አደገኛ' አድርጎ በመሳል፣ ግፍና በደል ሲፈጸምበት ሕዝቡ በዝምታ እንዲያልፍ ወይም የጥቃቱ ደጋፊ እንዲሆን የሚያደርግ የሞራል ድንዛዜ የመፍጠር ሴራ ነው።

3. የማህበረሰቡን ስነ-ልቦናዊ በራስ መተማመን መሸርሸር፦
🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀🔀

ሙስሊሙ ዜጋ መሠረታዊ መብቶቹን ሲጠይቅ 'ታርጋ ይለጠፍብኛል' በሚል ስጋት ራሱን እንዲያገልና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያለው ተሳትፎ እንዲቀጭጭ የሚያደርግ ስውር የባርነት ቀንበር ነው።

ይህ የፍረጃ ፖለቲካ ዛሬ በሙስሊሙ ላይ ቢሰነዘርም፣ ሰለባው ግን መላው የኢትዮጵያ ህዝብና የሀገሪቱ አንድነት ነው። ምክንያቱም ጥላቻና ፍረጃ ቦታ ባገኙበት ምድር፣ የዜግነት መብትና የህግ የበላይነት ሊከበር አይችልም። በመሆኑም ይህንን የሐሰት ትርክት መመከት የሙስሊሙ ማህበረሰብ ድርሻ ብቻ ሳይሆን፣ ለፍትህና ለሰው ልጅ ክብር የሚቆሙ የሁሉም እምነት ተከታዮችና ኢትዮጵያውያን የጋራ የዜግነት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል።

የጥቃቱ ስልታዊ ይዘት እና የምልክት ጦርነት
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺

ይህ የሥነ-ልቦና ጦርነት የሚካሄደው የማሰብ ሂደትን በማዛባት "ውሸትን እውነት" የማስመሰል ስልታዊ ተንኮልን በመጠቀም ነው። ሂደቱ ማስረጃን በፍረጃ የመተካት ጥበብ ሲሆን፤ የሚከተሉትን ሦስት የጥፋት ደረጃዎች ይከተላል፦

1. መረጃን መቆንጸል (Selective Filtering)፦
🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎

አንድን ክስተት ሙሉ በሙሉ ከመተንተን ይልቅ፣ ለፍረጃው የሚመቸውን ክፍል ብቻ ነጥሎ በመውሰድና አውዱን በማዛባት የጥላቻ ትርጉም መስጠት። ይህም ተደራሲው ግማሽ እውነትን ይዞ ሙሉ ስዕል ላይ እንዲደርስ የሚያደርግ የአእምሮ ጠለፋ ነው።

2. የምልክት ጦርነት ፦
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

በምልክት ጦርነት ውስጥ፣ ሙስሊምነትን የሚገልጹ ሃይማኖታዊ ምልክቶች ከመንፈሳዊ ይዘታቸው ተላቀው የ"አደጋ"፣ የ"ጽንፈኝነት" ወይም የ"መጤነት" መለያ ተደርገው ዳግም ይተረጎማሉ።

3. የሐሰት ስምምነት ማመንጨት ፦
🍗🍗🍗🍗🍗🍗🍗🍗🍗🍗

በብዙ አጋጣሚዎች እንደሚስተዋለው፣ ጥቂት ግለሰቦች በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን በመጠቀምና በተፅዕኖ ፈጣሪዎች በመታገዝ እነዚህን የፍረጃ ትረካዎች በስፋት እንዲሰራጩ ያደርጋሉ። ይህም ፍረጃው በብዙሃኑ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ለማስመስል የሚደረግ የተቀነባበረ የዲጂታል ዘመቻ አካል ይመስላል፤ በዚህም ሌሎች "ብዙሃኑ ከተቀበለው ትክክል ቢሆን ነው" በሚል ስሜት ተነድተው የጥላቻው አካል እንዲሆኑ በር ይከፍታል።

እነዚህ የፕሮፓጋንዳ ስልቶች ተቀናጅተው በሚሠሩበት ጊዜ፣ ሂደቱ አብዛኛውን ጊዜ የሚከተለውን ግልጽ የሥነ-ልቦና ቅደም ተከተል ይከተላል፦

ፍረጃ → ፍርሃት → ጥርጣሬ → መገለል → ዝምታ → ወደ ዳር መገፋት

ይህ ሂደት የሚከተሉትን ደረጃዎች ያልፋል፦

1. ፍረጃ ፦
📺📺📺📺
በመጀመሪያ በአንድ ማህበረሰብ ወይም በወካዮቹ ላይ አንድ ስያሜ/ታርጋ ይለጠፋል።

2. ፍርሃት ፦
🏡🏡🏡🏡

የተለጠፈው ታርጋ በማህበረሰቡ ውስጥ ስር የሰደደ ፍርሃትን ይፈጥራል።

3. ጥርጣሬ፦
📣📣📣📣
ፍርሃቱ ቀስ በቀስ ወደ እርስ በርስና ወደ ውጭ ጥርጣሬ ይቀየራል።

4. መገለል ፦
🎁🎁🎁🎁
ጥርጣሬው ማህበረሰቡ ከሌላው ወገን ጋር ያለው ግንኙነት እንዲቋረጥና ማህበራዊ መገለል እንዲፈጠር ያደርጋል።

5. ዝምታ ፦
🆔🆔🆔
መገለሉ በማህበረሰቡ ውስጥ የራስ-ሳንሱርንና ድምፅን የማጥፋት (ዝምታን የመምረጥ) ስሜት ይወልዳል።

6. ማግለልና ወደ ዳር መገፋት ፦
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
በመጨረሻም ኢላማ የተደረገው ማህበረሰብ ከሀገራዊ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ተገፍቶ ወደ ዳር እንዲወጣ ይደረጋል።

የፍረጃ ፖለቲካው ታሪካዊ ዳራ እና አዲሱ አካሄድ
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒

'ወሃቢያ' የሚለው ፍረጃ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ምኅዳር ውስጥ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን፣ ሙስሊሙን ከሀገራዊ ባለቤትነት ለማግለል ሲለጠፉ የቆዩት ጥረቶች ቅጥያ ነው። ይህ ሂደትም ሁለት ዋና ዋና ምዕራፎችን አልፏል፦

1. ባዕድ የማድረግ ጥንታዊ ስልት፦
🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮

ቀደም ባሉ ዘመናት ሙስሊሙን እንደ 'መጤ' ወይም 'ሰርጎ ገብ' አድርጎ የመሳል ስራ ይከናወን ነበር። ዓላማው ሙስሊሙ ከሀገሩ ጋር ያለውን ትስስር እና ለሀገሩ የከፈለውን መስዋዕትነት በመካድ ከሀገራዊ ውሳኔ ሰጪነት የማግለል ጥረት ነው።

2. ዓለም አቀፋዊ ፍረጃን የማላመድ ስልት፦
🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀

በዚህ ዘመን ደግሞ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የሚጠቀሰውን 'የጸረ ሽብርተኝነት ጦርነት' አውድን እንደ ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም፣ የቀድሞው 'ባዕድ የማድረግ' ስልት ከዘመኑ ጋር በሚመች መልኩ በ'ወሃቢዝም'፥ “አክራሪ”፥ “ጽንፈኛ”፥ “አይሲ ስ” ወዘተ በሚሉ ተለውጦ ይተገበራል። ይህ ስያሜ ሙስሊሙን ከሀገር በቀል ማንነቱ ነጥሎ 'የባዕድ አጀንዳ ተላላኪ' አስመስሎ ለጥቃት የሚያመቻች ስልታዊ ጥረት ነው።

የፍረጃው መሪ ተዋናዮች እና አጀንዳዎቻቸው
🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨

በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ "ወሃቢ"፣ "አክራሪ" ወይም "አሸባሪ" የሚሉ የፍረጃ ቃላትን ደጋግመው በሚለጥፉ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በብዙ አጋጣሚዎች የሚስተዋል አንድ ተደጋጋሚ ድርጊት አለ፤ ይኸውም አንዳንድ የተደራጁ አካላት በብሔርና በእምነት ፖለቲካ ስም የተቀነባበሩ የዲጂታል ዘመቻዎችን ሲያካሂዱ ይስተዋላል።

እነዚህን የፍርጃ ቃላት የሚፈጥሩ፣ መልእክቶችን የሚለጥፉና የሚያጋሩ ጥቂት ግለሰቦችን የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ስንመለከት የሚከተሉትን ሁለት ግልጽና ልዩ መለያዎችን እናያለን፦

1. የፖለቲካ አርማ ፦
🏀🏀🏀🏀🏀
በብዙዎቹ የእነዚህ አካላት ገጾች ላይ የሚስተዋሉ ተደጋጋሚ ምልክቶች አሉ፤ ለምሳሌ የፋኖ ደጋፊነትን የሚያሳዩ ምልክቶችና የጽንፈኛ ብሔርተኝነት መፈክሮች በስፋት ሲንጸባረቁ ይታያል።

2. ሃይማኖታዊ ሽፋን ፦
🚛🚛🚛🚛🚛🚛

ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ጋር የተቆራኙ ምልክቶችን እንደ መሸፈኛ በመጠቀም፣ የእምነቱን የሰላምና የአብሮነት እሴቶች የማይወክል የፖለቲካ ጥላቻን የሚረጩ ናቸው።

በፍርሃት ላይ የተመሠረተ የሕዝብ ንቅናቄ
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

እነዚህ አካላት የጋራ መለያቸው ማንኛውንም ሃይማኖታዊና ብሔራዊ ስሜት ቀስቃሽ ጉዳዮችን በመጠቀም በሕዝብ ዘንድ ፍርሃትን መፍጠር እና በዚያ ፍርሃት አማካኝነት ሕዝብን ለራሳቸው ስውር አጀንዳ ማሰለፍነው። በዚህ አካሄድ ላይ ተሰማርተው የምናገኛቸው ሦስት ተዋናዮች ናቸው። እነርሱም፦

1. ጽንፈኛ የብሔር ፖለቲከኞች ፦
💥💥💥💥💥💥💥💥💥

በብዙዎቹ የእነዚህ አካላት ገጾች ላይ የሚስተዋሉ ተደጋጋሚ ምልክቶች አሉ፤ ለምሳሌ፦ የፋኖ ደጋፊነትን የሚያሳዩ አርማዎች፣ ፎቶዎችና የጽንፈኛ ብሔርተኝነት መፈክሮች በስፋት ሲንጸባረቁ ይታያሉ። ይህም ፖለቲካዊ አጀንዳን ከሃይማኖታዊ ፍረጃ ጋር በማቀላቀል ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለጥቃት ኢላማ የማድረግ ስልት አካል ይመስላል። እነዚህ አካላት በዛ የሚሉቱ በአማራ በተለይ በፋኖ ጉዳይ እንንቀሳቀሳለን የሚሉ ሲሆኑ ስልታቸውም ሙስሊሙን ማህበረሰብ "የኦሮሞ ብልጽግና ስርዓት ስልታዊ አጋር" አድርጎ በመፈረጅ ለጥቃት ኢላማ ሲያደርጉት ይታያሉ።ከዚህ የተነሰ «ኦሮሙማ» እና «ስልጤ» የሚሉ ታፔላዎችን በመለጠፍ ሲፈርጁም ይታያል።

2. በእምነት ስም የሚንቀሳቀሱ አክራሪዎችና፦
🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀🚀

እነዚህ አካላት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ምልክቶችን እንደ መስቀልና የቅዱሳን ሥዕላትን እንደ መሸፈኛ በመጠቀም፣ የእምነቱን የሰላምና የአብሮነት እሴቶች የማይወክል የፖለቲካ ጥላቻን ይረጫሉ። ዋና ዓላማቸውም ታሪካዊ የበላይነትን ለማስጠበቅ ሲሉ የሙስሊሙን ማህበረሰብ መሠረታዊ የመብት ጥያቄዎች እንደ "ሕልውና ስጋት" አድርጎ ማቅረብ ሲሆን፣ ይህም ሙስሊሙን እንደ "መጤ" ወይም "የባዕድ አስተሳሰብ ተላላኪ" አድርጎ በመፈረጅ ከሀገር ባለቤትነት የማግለል ስልታዊ አካሄድ ነው።

እነዚህ አካላት ቤተ ክርስቲያንን እንደ ብቸኛ የሀገር ባለቤት አድርገው በመሳል የሚረጩት ይህ መርዛማ ትርክት፣ ተራው አማኝ የጥላቻ መልእክቱን እንደ ሃይማኖታዊ እውነት እንዲቀበለው በማድረግ ለዘመናት የቆየውን የሕዝቦች አብሮነት የሚሸረሽርና በዜጎች መካከል የጥርጣሬ ግንብ የሚገነባ አደገኛ ስልት ነው።

3. ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የ አካውንቶች ፦
🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎

በውጭ ሀገር የሚገኙና በዛ ያሉ ተከታዮች ያሏቸው የቲክቶክ፣ የቴሌግራም እና የፌስቡክ «መምህር»ና «አንቂዎች» የሚባሉ የዘመቻው ሞተሮች ናቸው። እነዚህ አካላት የተከታዮቻቸውንና የዓለም ዓቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ለመሳብ "በኢትዮጵያ የእስልምና አክራሪነት ስጋት ደቅኗል" የሚል አጀንዳ በመቅረጽ የጥላቻ ንግግሮችን በማቀናበር ሙስሊሞች ላይ ጥርጣሬና ፍርሃት እንዲነግስ ይተጋሉ።

የጠላት ፈጠራ ፋብሪካ፦ ስልታዊ ኪሳራ እና የማግለል ሴራ
🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡🏡

የእነዚህ አካላት ሌላኛው አደገኛው ጠባይ ይታይባቸዋል።ማንም ይሁን ማን በማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ዉስጥ እነርሱ የሚያዜሙትን ካላዜመ፥ በለቅሶ ፖለቲካቸው ላይ ከእነርሱ ጎን ተሰልፎ አብሮ ካላለቀሰ፥ ወይም ደስታውንም ሆነ ሀዘኑን እነርሱ ካሰመሩት አካሄድ ወጥቶ በራሱ መንገድ ጉዳዩ ላይ አቋሙን ከገለጸ ወይም ጥያቄ ካነሳ ፥አልያም ስልታዊ አካሄዳቸውንና ሴራቸውን ካወቁባቸው ወይም ድጋፍ ካነፈጓቸው ወዲያውኑ "የአማራ ጠላት" ወይም "የኦርቶዶክስ ጠላት" የሚሉ የታፔላዎች ተመዘው ይለጠፍበታል።

በዚህ አካሄዳቸው የተነሳ ለአማራ ሕዝብ እና ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን በቀንና በሌሊት በርካታ «ጠላቶችን» እየፈጠሩ ይገኛሉ። ባለፉት ሰባት ዓመታት ብቻ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻቸው እንደታዘብኩት በርካታ አካላትን ጠላት በሚል ፈርጀው ዘምተውባቸዋል።

በአማራ ክልል ውስጥ የቅማንትን፣ የአገውን፣ የወሎ ኦሮሞን፣ አማራ ሙስሊሙንና የክልሉን መንግሥት (በብአዴን ስም)፤ በወሎ ሕዝብ ጉዳይ የሚንቀሳቀሱ አካላትን፥ ከክልል ውጭ ደግሞ መላው የኢትዮጵያ ሙስሊምን ("ወሃቢ" በሚል)፣ የትግራይ ኤሊትንና ፓርቲን፣ እንደሕዝብ የኦሮሞንና የስልጤን ሕዝብ፣ በመተከል ያሉ የቤኒሻንጉል ብሔረሰብ አባላትን፥ከፓርቲ ደግሞ የብልጽግና ፓርቲን፥ኢዜማን፥ በጠላትነት ፈርጀዋል። በግለሰብ ደረጃ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩን፥ ጀውሃር መሀድን፥ እኔ አሕመዲን ጀበልን ጨምሮ በርካቶችን ሲፈርጁ ታዝቤያለሁ።

እዚህ ላይ አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ማንሳት ያስፈልጋል። ለመሆኑ በቀን 24 ሰዓት ስድብን፣ ፍረጃንና ጠላትን ማምረት እነርሱ ቆመንለታል ለሚሉት ለአማራም ሆነ ለኦርቶዶክ እምነት ተከታይ ሕዝብ ምን ጥቅም ያስገኝላቸዋል? የሕዝቡን ዘላቂ ችግሮች ይፈታል ወይስ ይበልጥ ያባብሳል?

ከወዳጅ ይልቅ ጠላትን ማምረት የፖለቲካ ብስለት ሳይሆን ስልታዊ ኪሳራ ነው። ለአማራ ሕዝብም ሆነ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ትክክለኛው ስልታዊ ጥቅም የሚገኘው ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር አጋርነትና ጥምረትን በመፍጠርና ድጋፍ በማሰባሰብ እንጂ ጠላትን በማብዛት አልያም ስድብ የሚያዋጡ በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን በመፍጠር አይደለም።

ከየትኛውም ወገን ይሁን ከየት የሚሰነዘርባቸውን ጥቃቶች ለመመከትና የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ትኩረትና ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙ የሌሎችን ወገኖች አጋርነትና ድጋፍ ማግኘት እጅግ ወሳኝ ነው። በተጨማሪም ሁሉንም ወገን በጠላትነት መፈርጅና ማግለል የፍትሕ ጥያቄያቸው ድጋፍ እንዳያገኝ በማድረግ ለብቻቸው ተነጥለው ለጥቃት እንዲጋለጡ በማድረግ የከፋ ጉዳት ያመጣል።

እነዚህን የጥላቻ ትረካዎች የሚያመርቱ፣ በጅምላ የሚፈርጁና በየቀኑ ጠላት የሚፈጥሩ አካላት በማንኛውም መልኩ ሊደገፉ፣ ሊበረታቱ ወይም የትግሉ አካል ሊደረጉ አይገባም። የእነሱ ድርጊት የሕዝቡን ስቃይ የሚያራዝም እንጂ መፍትሔ የሚያመጣ ባለመሆኑ፣ ይህ አካሄድ የጠላት ተግባር እንጂ የወዳጅ እርምጃ ሊባል አይችልም።

ከዚህም ባለፈ፣ በሌሎች ሃይማኖታዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ተቋማትና እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር እነሱን ለማጥቃት ጊዜን ማጥፋት ፈጽሞ ትክክለኛ አካሄድ ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም በሌሎች ላይ ስታተኩር ሌሎችም በአንተ ላይ እንዲያተኩሩ በሩን እየከፈትክ መሆኑን መዘንጋት የለብህም። ሌሎች ላይ በከፈትከው ግንባር ልክ አጸፋው ወደ አንተ እንደሚመለስና ለራስህ ተቋማትና እሴቶች ስጋት እንደሚሆን የታወቀ ነው።

የጥቃቱ ኢላማዎች እና ስልታዊ ስኬቶች
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

ይህ የተቀነባበረ ዘመቻ በዘፈቀደ የሚሰነዘር ሳይሆን፣ ማህበረሰቡን 'መሪ አልባ' በማድረግ በምሁራንና በተቋማት ላይ እምነት በማሳጣት ስልታዊ ውድመት ለማድረስ የታለመ ነው። ፕሮፓጋንዳ ነጋዴዎቹ የሚከተሉትን ሦስት ዋና ዋና ስኬቶች ለመቀዳጀት ይጥራሉ፦

1. መጤ አድርጎ የመሳል ሴራ
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺
እስልምናን እንደ 'ባዕድ አስተሳሰብ' በመሳል ሙስሊሙን ከሀገሩ ታሪክ ጋር ያለውን ትስስር ለመበጠስ ይሰራሉ። ዓላማው ማህበረሰቡን በመበታተን በገዛ ሀገሩ እንደ እንግዳ እንዲቆጠር ማድረግ ሲሆን፣ ይህም ሙስሊሙ መሠረታዊ መብቱን ሲጠይቅ እንደ 'የባዕድ አጀንዳ' ተቆጥሮ ውድቅ እንዲደረግና ለማህበረሰባዊ አንድነት እንቅፋት እንዲሆን ታስቦ የሚከናወን ነው።

2. ከፍረጃ ወደ ፈቃድ ማውጫ
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

ንጹሐን ሙስሊሞች ላይ የሚፈጸሙ ዘግናኝ ጥቃቶችን 'ጽንፈኞችን የማጽዳት እርምጃ' አስመስሎ በማቅረብ፣ ለጥላቻና ለጥቃት ማኅበራዊ ፈቃድ ለማግኘት ይጣራል።ግፍ ሕጋዊ ከመደረጉ በፊት፣ ጥላቻ ማህበራዊ ተቀባይነት እንዲያገኝ ይደረጋል። ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት ሰለባው በጥርጣሬ እንዲታይ ይደረጋል።
3. የዓለም አቀፍ ድጋፍ መሸጫ
'ወሃቢዝም' እና 'ሽብርተኝነት' የሚሉ ስሜት ቀስቃሽ ቃላትን እንደ መሸጫ መሣሪያ በመጠቀም፣ ከምዕራባውያንና ከዓለም አቀፍ አካላት ዘንድ የፖለቲካና የፋይናንስ ድጋፍ ለማግኘት የሐሰት ትርክት ይሰራሉ። ይህ ስሌት በሀገር ውስጥ ያሉ ምሁራንና ተቋማት ላይ ዓለም አቀፍ ጫና እንዲፈጠር በማድረግ፣ ማህበረሰቡን የሚመራበት አስተማማኝ አቅጣጫ በማውጣት ለጥላቻ ነጋዴዎች ስውር የፖለቲካ ፍላጎት ተገዢ እንዲሆን ያደርገዋል።

ሂደቱ በሚከተለው መልኩ ወደ አደገኛ ደረጃ ይሸጋገራል፦

ተደጋጋሚ ክስ → ማኅበራዊ መላመድ → የሞራል ድንዛዜ → የማግለል ፈቃድ

ይህ የጥፋት ጉዞ የሚከተሉትን ደረጃዎች ይይዛል፦

1. ተደጋጋሚ ክስ
✅✅✅✅✅✅

አንዱን ወገን ኢላማ ያደረጉ የሐሰት ትርክቶችና ፍረጃዎች በማኅበራዊ ሚዲያና በተለያዩ አውታሮች ደጋግመው ይለቀቃሉ።

2. ማኅበራዊ መላመድ
📶📶📶📶📶📶📶

ክሱ በየቀኑ ሲደጋገም፣ መጀመሪያ ላይ "እውነት አይደለም" ብሎ ሲሞግት የነበረው ማህበረሰብ ቃላቱንና ትረካዎቹን እንደ ተራ ወሬ መልመድ ይጀምራል።

3. የሞራል ድንዛዜ
🌲🌲🌲🌲🌲

ማህበረሰቡ ፍረጃውን ሲለምደው፣ በተበዳዩ ወገን ላይ ለሚፈጸሙ ግፎችና መገለሎች ያለው ርኅራኄ እየቀነሰ ይሄዳል። "ሊደረግበት የሚገባው ነው" የሚል የሞራል ድንዛዜ ውስጥ ይገባል።

4. የማግለል ፈቃድ
📦📦📦📦📦📦
በመጨረሻም፣ ግለሰቡን ወይም ማህበረሰቡን ከሀገራዊና ማኅበራዊ ተሳትፎ ማግለል፣ አልፎም ጥቃት መፈጸም በዝምታ የሚታለፍ አልፎም የሚደገፍ "ሕዝባዊ ይሁንታ" ያገኛል።

የሥነ-ልቦና ሽባነት እና የውስጥ ክፍፍል
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የዚህ ስልታዊ ዘመቻ ስር የሰደደ ግብ ሙስሊሙን ማህበረሰብ በሥነ-ልቦና ደካማ፣ በውስጥ የተከፋፈለ እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ድምፅ አልባና የተገለለ (Marginalized) ማድረግ ነው። ይህ ግብ የሚሳካው ማህበረሰቡን ለሚከተሉት ሶስት አደገኛ ጫናዎች አሳልፎ በመስጠት ነው፦

1. ራስን መገደብ
🍎🍎🍎🍎🍎

የፍረጃው ቀዳሚ ውጤት ሙስሊሙ ዜጋ "ጽንፈኛ፣ ወሃቢ ወይም አክራሪ ልባል ነው" በሚል ስጋት ራሱንና ሃሳቡን እንዲገታ ማድረግ ነው። ለምሳሌ፦ አንድ ሙስሊም በሥራ ቦታው፣ በዩኒቨርሲቲው ወይም በፖለቲካው መድረክ መሠረታዊ መብቱን ሲያስከብር ወይም ሙያዊ ብቃቱን ሲያሳይ "ታርጋ ይለጠፍብኛል" በሚል ስጋት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል። ይህ ሥነ-ልቦናዊ ሽባነት ግለሰቡ በሀገሪቱ የለውጥና የልማት ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዳይሆን በማድረግ፣ የማህበረሰቡን ሀገራዊ አበርክቶ ያኮላሻል።

2. የገጽታ ጥቃት
📣📣📣📣📣

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚያነሳቸውን ፍትሐዊና አመክንዮአዊ ጥያቄዎች በሐቅ መመለስ ሲያቅታቸው፣ ብቸኛው መሸሸጊያቸው ጥያቄውን ሳይሆን ጠያቂውን ማጥቃት ነው። ይህም በኡስታዞችና በመሪዎች ላይ የተመረዙ ትረካዎችን በመርጨት ስማቸውን ማጠልሸት ነው። የዚህ የገጽታ ግድያ ስልት ዋና ዓላማ በመሪውና በተከታዩ መካከል ያለውን "የመተማመን ድልድይ" በመስበር፣ ማህበረሰቡን መሪ አልባና አቅጣጫ የለሽ አድርጎ ማስቀረት ነው።

3. የውስጥ ክፍፍል (ከፋፍለህ ግዛ)
♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦

ማህበረሰቡን በ"ነባር" እና "መጤ" ወይም በ"ሱፊ" እና "ወሃቢ"/«ሰለፊ» በሚሉ ጎራዎች ተቧድኖ በውስጥ ንትርክ እንዲጠመድ የማድረግ ፍላጎትና አካሄድ እንዳላቸው በተደጋጋሚ ተስተውሏል። የሙስሊሞችን ጉዳዮችን በዚህ መነጽር ብቻ እንዲታይ ደጋፊ ሚዲያዎቻቸው ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርጉ ታዝበናል። ይህም ፍላጎታቸውን አላረካ ሲልም አንዱን ቡድን ደግፈው በመጅሊስ ጉዳይና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ይመለከተናል በሚል ቃና በግልጽ ሲታገሉም ታይተዋል።

ማህበረሰቡ በውስጣዊ ልዩነቶች ላይ እንዲያተኩር ሲደረግ፣ በጋራ በሚሰነዘሩበት በደሎችና ስልታዊ አደጋዎች ላይ አብሮ የመቆም አቅሙ ይዳከማል። ይህ የውስጥ መከፋፈል ማህበረሰቡን ለውጭ ጥቃትና ለፖለቲካዊ መጠቀሚያነት ተገላጭና ምቹ ያደርገዋል።
በአጠቃላይ እነዚህ ስልቶች ሲቀናጁ ማህበረሰቡ በገዛ ሀገሩ ላይ ባይተዋርነት እንዲሰማው፣ ለጋራ ጥቅሙ እንዳይቆም እና በሥነ-ልቦና ተሸንፎ ለሌሎች ፍላጎት ተገዥ እንዲሆን የተሰናዱ የወጥመድ ፖለቲካ መገለጫዎች ናቸው።

ያልተደነገገው «ወንጀል» እና የቃላት ላቦራቶሪ
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ውስጥ "ወሃቢ"፣ "አክራሪ" ወይም "ጽንፈኛ" የሚባል የወንጀል ዓይነትም ሆነ ድንጋጌ የለም። እነዚህ ቃላት በሕግ መጻሕፍት ውስጥ የማይገኙ፣ ነገር ግን በፕሮፓጋንዳ ነጋዴዎች ላቦራቶሪ ውስጥ ለሥነ-ልቦና ጦርነት መሣሪያነት የተፈበረኩ የፖለቲካ ማጥቆሪያ ታርጋዎች ናቸው። ዓላማቸውም ማህበረሰቡን በህግ ጥላ ስር ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ ጥላቻ ስር እንዲወድቅ በማድረግ የሞራል ልዕልናውን መንካት ነው።

የጥላቻ ትረካ ስርጭት ወቅታዊ ስሌቶች
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የፕሮፓጋንዳ ነጋዴዎቹ የጥላቻ መርዛቸውን የሚረጩባቸው ወቅቶች በዘፈቀደ የሚመረጡ ሳይሆኑ፣ ከፍተኛ ሥነ-ልቦናዊ ድንጋጤ ለመፍጠር ታስበው በሚከተሉት ሦስት ስሌቶች የሚሰናዱ ናቸው፦

1. የፀጥታ ችግሮችን ለሴራ መጠቀም
🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀

በሀገሪቱ የትኛውም አካባቢ የፀጥታ መታወክ ሲከሰት፣ ያለ ምንም ማስረጃ "የወሃቢ እጅ አለበት" የሚሉ ትረካዎችን በማሰራጨት ሙስሊሙን ከስጋት ጋር በማቆራኘት በሕዝብ ዘንድ ጥርጣሬን መዝራት።

2. የፖለቲካ ጦስ
📦📦📦📦📦
ሀገራዊ የፖለቲካ ውጥረቶች ሲበረቱና የሕዝብ ጥያቄዎች ሲገዝፉ፣ የሕዝቡን ትኩረት አቅጣጫ ለማስለወጥ ሙስሊሙን ማህበረሰብ እንደ ማላከኪያ በመጠቀም የጥላቻ ግንባር መክፈት።

3. በሃይማኖታዊ በዓላት ላይ የሚሰነዘር ጥቃት
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶

የጁምዓ ተቃውሞዎች፥ እንደ ረመዳን እና ኢድ ባሉ ታላላቅ በዓላት ወቅት የሚከናወኑ በጎ አድራጎቶችን እንኳ "ለጽንፈኝነት ምልመላ" እንደዋሉ በመሳል፣ በበዓላቱ ድምቀት ላይ የጥርጣሬና የፍርሃት ድባብ መፍጠር።የወጣቶች ካውንስል የአባልነት ምዝገባም ሆነ የአደባባይ ኢፍጣሮችም በዚሁ መልኩ ፈርጀዋቸዋል።

እነዚህን የ"ትኩረት ጠለፋ" ስልቶች መረዳት፣ ጥቃቱ ሲሰነዘር በስሜት ከመነዳት ይልቅ በዕውቀት ለመመከት ያስችላል። መብት የችሮታ ውጤት ሳይሆን የዜግነት መገለጫ መሆኑን ማመን የጽናታችን ምንጭ ሊሆን ይገባል።

ይህ ለምን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ያሳስባል?
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅

የታርጋ ፖለቲካና የጅምላ ፍረጃ ዛሬ በአንድ ወገን ላይ ቢሰነዘርም፣ ነገ ግን መላውን ሀገርና የዜግነት መብትን የሚንድ የጋራ ጠላት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። ይህንን የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ መመከት የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ ለፍትሕና ለሰው ልጅ ክብር የሚቆሙ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ግዴታ ነው።

ለዘመናት የጸናው የአብሮነትና የሰላም እሴታችን በጥቂት አንቂዎች የፈጠራ ትረካና በዲጂታል ሴራ ፈጽሞ ሊፈርስ አይችልም። በመሆኑም እውነትን በማንገብ የሐሰትን ወጥመድ በመበጣጠስ ፣ የሁላችንም መሸሸጊያ የሆነችውን ኢትዮጵያን ከፍረጃና ከጥላቻ ፖለቲካ ነፃ ማውጣት ታሪካዊ ኃላፊነታችን ነው። ለዛሬ አበቃሁ። ቸር እንሰንበት!

Address

P. O. Box 1696
Kella
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nur Broadcast posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share