አደይ

አደይ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አደይ, Arts and entertainment, Any Where, Addis Ababa.
(2)

ዘሃበሻ የዉሸት ቋት! ከሰሞኑን በተከታታይ በቴዲ አፍሮ ዙሪያ በተከታታይነት ሰዎች ታሰሩ ምክትል ማኔጀሯ የቴዲ የቅርብ ጓደኛዉ ተወሰደ፤ ስቱድዮዉ ተሰበረ፤ ከለሊቱ 6: ሠዓት በቴዲ አፍሮ መኖ...
26/04/2026

ዘሃበሻ የዉሸት ቋት!

ከሰሞኑን በተከታታይ በቴዲ አፍሮ ዙሪያ በተከታታይነት ሰዎች ታሰሩ ምክትል ማኔጀሯ የቴዲ የቅርብ ጓደኛዉ ተወሰደ፤ ስቱድዮዉ ተሰበረ፤ ከለሊቱ 6: ሠዓት በቴዲ አፍሮ መኖሪያ ቤት ፌዴራል ፖሊሶች ሄዱ እያለ ዘገባ ሲሰራ የነበረዉ በሙሉ ዉሸት መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ በሰጠዉ መግለጫ መረዳት ተችሏል።

ይኸዉም በቴዲ አፍሮ ዙሪያ ምንም የተጀመረ ክስም እየተጣራ ያለ አንዳች ጉዳይ አለመኖሩን ፌዴራል ፖሊስ በመግለጫዉ አስታዉቋል።

"በቴዲ አፍሮ ላይ የተሰራ ምንም አይነት የወንጀል ምርመራ የለም" - ፌዴራል ፖሊስ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከሰሞኑ በተወዳጁ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ (ቴዎድሮስ ካሳሁን) ላይ እየደረሰ ነው ስለተባለው ጫና፣ ዝርፊያ እና ወከባ የቀረቡ መረጃዎች መሰረተ ቢስ መሆናቸውን በመግለጽ ማብራሪያ ሰጥቷል።

የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምርያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት፣ ፖሊስ በአርቲስቱ ላይ የከፈተው ምንም አይነት የምርመራ መዝገብም ሆነ እያከናወነ ያለው የክትትል ስራ የለም።

አቶ ሙሊሳ በማብራሪያቸው "የፌደራል ፖሊስ እንደዚህ አይነት ውንብድና አይሰራም፤ ስብዕናውም አይደለም። የሚሰራው በህግና በህግ ብቻ ነው" ብለዋል። አርቲስቱ በአሁኑ ወቅት የፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪ እንዳልሆነና በእሱ ላይ የሚከናወን ምንም አይነት ኦፕሬሽን እንደሌለ አጽንኦት ሰጥተዋል። "አርቲስቱ ቤቱ ነው ያለው፤ በስርዓት እየኖረ ነው፤ በእሱ ላይ የተደረገ ምንም አይነት ነገር የለም" ሲሉ አክለዋል።

በአርቲስቱ ላይ "ዝርፊያ ተፈጽሟል፣ የሙዚቃ መሳሪያዎቹ ተወስደዋል፣ መግለጫ እንዳይሰጥ ተከልክሏል" በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች በሙሉ "የፈጠራ ወሬዎች" መሆናቸውን የገለጹት ሃላፊው፣ ድርጊቱን "አርቲስቱን እንደማስያዣ በመጠቀም የፖለቲካ አጀንዳ ለማራገብና ህዝብ ላይ ሽብር ለመፍጠር የሚደረግ የሳይበር ወሬ" ሲሉ ጠርተውታል።

"ይሄ ዜጋ ህገመንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ሙዚቃ ሰርቷል። አርቲስት ሆኖ ሙዚቃ መስራት እና የፈለገውን አመለካከት የመያዝ ህገመንግስታዊ መብት አለው። ከዚህ ውጪ ያለ ማስረጃ ሰው የማይያዝበትን አሰራር ፈጥረናል" ብለዋል።

አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ህዝቡ በየቀኑ የሚፈጠሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሀሰት ወሬዎችን ከማመን እንዲቆጠብና መረጃዎችን እንዲያመዛዝን ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም በቴክኖሎጂ (AI) የታገዙ የሀሰት መረጃዎች ስጋት መሆናቸውን በመጠቆም፣ የጸጥታ ተቋሙ ማንኛውንም የምርመራ ስራ ሲሰራ በግልጽ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጸዋል።

በመጨረሻም "ወንጀል የሰራ ማንም ሰው (የመንግስት አካልም ቢሆን) በህግ ይጠየቃል፤ ወንጀል ያልሰራ ሰው ግን በፍጹም አይጠየቅም" ሲሉ የፖሊስን አቋም በድጋሚ አረጋግጠዋል።

የ75 አመት አዛዉንት እናትን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ በኣሪ ዞን በባካ ደውላ ኣሪ ወረዳ ጌዛ ቀበሌ በአንዲት የ75 ዓመት አዛዉንት እናት ላይ አስገድዶ ...
25/04/2026

የ75 አመት አዛዉንት እናትን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ

በኣሪ ዞን በባካ ደውላ ኣሪ ወረዳ ጌዛ ቀበሌ በአንዲት የ75 ዓመት አዛዉንት እናት ላይ አስገድዶ የመድፈረ ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በፅኑ እስራት መቀጣቱን የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ወንጀሉ የተፈጸመዉ ጥር 17/2018 ዓ.ም በወረዳዉ ጌዛ ቀበሌ በተለምዶ ማዊ ተብሎ በምጠራ አካባቢ ሲሆን ተከሳሽ ወጣት ታምራት ታደለ የተባለው ግለሰብ በግምት ከሌልቱ 7፡00 ሰዓት ላይ የግል ተበዳይ ወ/ሮ ቃሽቶ አይሚ የተባለችዉን የ75 ዓመት አዛዉንት በመኖሪያ ቤታቸው በተኙበት መስኮት ሰብሮ በመግባት ድርጊቱን መፈፀሙን በክሱ መዝገብ ላይ ተጠቅሷል።

የባካ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ፖሊስ ግለሰቡ ወንጀሉን ስለመፈጸሙ አቤቱታ ካቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማሰባሰብ ምርመራውን አጣርቶ ለአቃቤ ህግ አቅርቧል።

ዐቃቤ ህግ ፣ ተከሳሹ አዛውንቷ ራሷን መከላከል እንደማትችል አዉቆ መስኮቱን ሰብሮ በመግባት መከላከል በማትችልበት ሁኔታ ድርጊቱን እንደፈፀመ የሚያስረዱ ማስረጃዎችን አስደግፎ ለወረዳዉ ፍርድ ቤት ክሱን አቅርቧል።

ክሱን ስመለከት የቆየው የወረዳው ፍርድ ቤት ዐቃቤ ህግ ያቀረበውን ማስረጃ ግራ ቀኝ በመመልከት ተከሳሽ ወጣት ታምራት ታደለ የተባለው ግለሰብ የፈፀመውን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ድርጊት በምስክር እና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጥ ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹ በ 12 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድቤቱ ወስኗል።

የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እና የችሎቱ ዳኛ የሆኑት አቶ መለሠ ጋልሺ ባስተላለፉት መልዕክት የቅጣት ውሳኔዎች ዋና ዓላማ ህግ በወንጀል እንዳይጣስ እና ለሎች ዜጎች ከወንጀል ድርጊት እንድታቀቡ ለማስተማር እንደሆነም አስገንዝበዋል።

በሴቶችና ህፃናት ላይ እንዲሁም ራሳቸውን መከላከል በማይችሉ አቅመ ደካማ እናቶች ላይ የምፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ወንጀልን ለመከላከል ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ኃላፊነቱን ልወጣ እንደምገባም የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ልሳኑ በመልዕክታቸዉ አሳስበዋል።

አንዷለም በ1 ቀን በ500ሺህ ተመልካች ቀዳሚ ሆነ🔥የነቀምቱ አንዷለም አስተመች ለሙከራ ያቀረበው የቤተሰብ ጨዋታ በሾው ታሪክ ከፍተኛ ቁጥርም ሆኗል። አንዷለም በአንድ ቀን ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ...
21/04/2026

አንዷለም በ1 ቀን በ500ሺህ ተመልካች ቀዳሚ ሆነ🔥

የነቀምቱ አንዷለም አስተመች ለሙከራ ያቀረበው የቤተሰብ ጨዋታ በሾው ታሪክ ከፍተኛ ቁጥርም ሆኗል። አንዷለም በአንድ ቀን ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ተመልካች ማግኘት ችሏል። ከዚህ ቀደም 600ሺህ ተመልካች ያገኘው ኮሜዲያን ያሲኖ ያንን ቁጥር ለማግኘት 9 ቀናት ወስዶበታል። አንዷለም በአንድ ቀን ተኩል የናሲኖን ሪከርድም ሰብሯል።

ከማሪ ማንሳ ወደ ታርጫ ይጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ የመገልበጥ አደጋ ደረሰበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ከማሪ ማንሳ ወረዳ ወደ ታርጫ ይጓዝ የነበረ የህዝብ...
19/04/2026

ከማሪ ማንሳ ወደ ታርጫ ይጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ የመገልበጥ አደጋ ደረሰ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ከማሪ ማንሳ ወረዳ ወደ ታርጫ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል። አሽገራሚው ነገር በሰው ላይ የከፋ ጉዳት አለመድረሱ ነው። ዝርዝር የጉዳቱ መጠን እየተጣራ ይገኛል።

ቤተክርስቲያኗ በከባድ መሣሪያ ተመታች። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በቆቦ ከተማ ቤተክህነት አስተዳደር የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በ...
16/04/2026

ቤተክርስቲያኗ በከባድ መሣሪያ ተመታች።

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በቆቦ ከተማ ቤተክህነት አስተዳደር የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአካባቢው በተከሰተ ጦርነት በከባድ መሣሪያ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፡፡

ቤተክርስቲያኑ በከባድ መሣሪያ ጉዳት ሲደርስበት በአገልግሎት ላይ የነበሩ ካህናት በእግዚአብሔር ጥበቃ ጉዳት ባይደርስባቸውም የጣራ ቆርቆሮ፣ ኮርኒስና መስታዎት ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ መሆኑን፤ መገልገያ አልባሳትና መጻሕፍቱ ደግሞ በከፊል መጎዳታቸውን ወረዳ ቤተክህነቱ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ሰበካ ጉባኤው የሕንጻ ቤተክርስቲያኑን የጉዳት መጠን በባለሙያዎች ለማስጠናት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡
የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን በምእመናን ድካምና በከፍተኛ ወጭ በጥርብ ድንጋይ ተገንብቶ ሰኔ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመርቆ እየተገለገሉበት የነበረ ሲሆን በደረሰው ጉዳት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አገልግሎቱን ለማስቀጠል መቸገሩን ገልጾ የፈረሰውን ለመጠገን በጎ አድራጊዎች ድጋፍ እንድያደርጉለት መንፈሳዊ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ለተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች በቅድሚያ የከበረ ሠላምታዬን እያቀረብኩኝ ላለፉት 27 ዓመታት ኢትዮጵያዊነትን በማፈንና ብሄራዊ ስሜትን በማደብዘዝ አገራችንን ለአደጋ ከዳረገው ስርአት ለመላ...
15/04/2026

ለተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች በቅድሚያ የከበረ ሠላምታዬን እያቀረብኩኝ ላለፉት 27 ዓመታት ኢትዮጵያዊነትን በማፈንና ብሄራዊ ስሜትን በማደብዘዝ አገራችንን ለአደጋ ከዳረገው ስርአት ለመላቀቅና በምትኩ አንድነትን ፥ መተባበርን እና ፍትህን ለማስፈን ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊነትን ለማዳን በተለያየ አቅጣጫ ብዙ እንቅስቃሴዎች በሚካሄድበት በአሁኑ ወቅት፦

በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ኢትዮጵያዊነትን እና ይቅር መባባልን ይዘው ብቅ ላሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድና ባልደረቦቻቸው አጭር በሚባል የስልጣን ቆይታቸው ለወሰዶቸው በጎ እርምጃዎች እና ላሳዩን ኢትዮጵያዊ አለኝታነት አጋርነትን ማሳየት እና ከጎናቸው መቆም ጊዜው የሚጠይቀው አስፈላጊ ተግባር መሆኑን ስገልፅ በሚደረጉት የድጋፍ እንቅስቃሴዎች ላይ በሥራ አጋጣሚ በቦታው ባልገኝም በመንፈስ አብሬያችሁ መሆኔን ሳረጋግጥ በታላቅ ኢትዮጵያዊ ስሜት ነው።

ድል ለኢትዮጵያዊነት
ፍቅር ያሸንፋል
ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)

June 19/2018

ፋርሴዎች የአምቦው 120 መንግስታዊ ማፊያ ቡድን በቁጥጥር ስር ውሏል የሚል የሀሰት ወሬ እያናፈሱ ነው። ውሸት ነው። ካሳዬ ቀነንሳን ጨመሮ የቡድኑ ዋና መሪዎች  እስካሁን አልተያዙም 1. ናኦ...
15/04/2026

ፋርሴዎች የአምቦው 120 መንግስታዊ ማፊያ ቡድን በቁጥጥር ስር ውሏል የሚል የሀሰት ወሬ እያናፈሱ ነው። ውሸት ነው። ካሳዬ ቀነንሳን ጨመሮ የቡድኑ ዋና መሪዎች እስካሁን አልተያዙም

1. ናኦል ኩምሳ ( ሊቀመንበር)፣ የምእራብ ሸዋ ዞን የብልጽግና ሚዲያ ቡድን መሪ
2. መንጌ ተፈሪ ( ምክትል)፣ በአምቦ ከተማ የ ያኢ ገዳ ቀበሌ ብልጽግና ፓርቲ ሊቀመንበር
3. ካሳዬ ቀነኒሳ (፣ የአፋኝ፣ ደባዲቢና ገዳይ ስቋድ መሪ
4. ዲናኦል ቃበታ፣ የድብደባውን ቪዲዮ በመቅዳት የሚያሰራጭ
5. ፍራኦል ፊቃዱ፣ የታርጌት ሰዎችን መልምሎ የሚያዘጋጅ

እነዚህ ማፊያዎች መያዙ ቀርቶ ትላንት ሌሊቱን በየቤቱ እየዞሩ የካቢኔ አባላትና ወጣቶችን በሚዳያ አጋለጣችሁን በማላት ሲያስፈራሩ ነበር። 7 ሰዎችንም ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረዋል።

ጃዋር መሀመድ

ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ከልጅነት እሰከ ዕዉቀት በፎቶ!
15/04/2026

ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ከልጅነት እሰከ ዕዉቀት በፎቶ!

በፋሲካ ዕለት ተ ደ ፍ ራ ተ ገ ድ ላ ተገኘች!💔👉እንድትደፈር ጓደኞቿ ሁኔታዎችን አመቻችተዋል ።በቴፒ ከተማ የፋሲካ እለት ሴት ጓደኞቿ አሳልፈው የሰጧት ወጣት ወይንሸት ተ ደ ፍ ራ ህይወቷ ...
14/04/2026

በፋሲካ ዕለት ተ ደ ፍ ራ ተ ገ ድ ላ ተገኘች!💔
👉እንድትደፈር ጓደኞቿ ሁኔታዎችን አመቻችተዋል ።

በቴፒ ከተማ የፋሲካ እለት ሴት ጓደኞቿ አሳልፈው የሰጧት ወጣት ወይንሸት ተ ደ ፍ ራ ህይወቷ አለፈ።

ወይንሸት ወዳጆ ትባላለች። ተወልዳ ያደገችው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሸካ ዞን የኪ ወረዳ ሾሻ ቀበሌ ቢሆንም ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ግን ቤተሰቦቿ መኖርያቸውን ቴፒ ከተማ ሠላም ቀበሌ ዳውሮ ሠፈር አድርገው መኖር ጀምረው ነበር።

ወይንሸት የፋሲካ ዕለት ከቀኑ 11:00 ሰዓት አካባቢ ከሁለት ጓደኞቿ ጋር በመሆን ለመዝናናት በሚል ከቤት እንደወጣች ሳትመለስ ትቀራለች።

የልጃቸው ቤት ያለመመለስ ያስጨነቃቸው አባት ያለ እንቅልፍ አደሩ። በማግስቱ ግን የሰሙት ዜና ከባድ ሀዘን እና ድንጋጤ ውስጥ ከተታቸው። ልጃቸው ወይንሸት ተ ደ ፍ ራ ተገድላለች።

ወንጀሉ የተፈጸመው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ በተለምዶ አሮጌው ቀበሌ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን ወንጀሉ መፈጸሙን መረጃ የደረሰው የቴፒ ከተማ ፖሊስ ብርቱ ክትትል በማድረግ ወንጀለኛውን ሾሻ ቀበሌ ዉስጥ ሰኞ ምሽት ላይ ከተሸሸገበት ስፍራ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የከተማዋ ፖሊስ መረጃ ያመለክታል።

ይህን አ*ሰ*ቃ*ቂ የወንጀል ድርጊት ፈፅሟል ተብሎ ከተያዘው መሀመድ በሽር ከሚባል ግለሰብ በተጨማሪ ለደፋሪው ተደራድረው አሳልፈው የሰጧት ሁለት የሴት ጓደኞቿም ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው የሚገኝ ሲሆን ለድርጊቱ ፈጻሚዎች ጠንከር ያለ የፍትህ ውሳኔ እንዲሰጥ የከተማዋ ነዋሪዎች እየጠየቁ እንደሚገኙ ተሰምቷል።

via:- ዶች ኤችዲ

የአንቦን ህዝብ ያስጨነቀው ማፍያው ካሳዬ ቀነኒሳ!  #አደይ:|  እጅግ ብዙ ቪዲዮዎችና ሜሴጆች ከአምቦ ነዋሪዎች ይርሱኛል። ብዙዎቹን ከፍቼ አላየኋቸውም ነበር። አሁን ግን ስመለከት አይኔን ማ...
14/04/2026

የአንቦን ህዝብ ያስጨነቀው ማፍያው ካሳዬ ቀነኒሳ!

#አደይ:| እጅግ ብዙ ቪዲዮዎችና ሜሴጆች ከአምቦ ነዋሪዎች ይርሱኛል። ብዙዎቹን ከፍቼ አላየኋቸውም ነበር። አሁን ግን ስመለከት አይኔን ማመን ነው ያቃተኝ። ይሄ በምስሉ ለይ የሚታየው ሰውዬ በተለያየ ግዜ የተለያዩ ሰዎችን እንደእንሰሳ ሲቀጠቅጥ የሚያሳይ ቪዲዮ ነው የደረሰኝ።

የሰውየው ስም ካሳዬ ቀነኒሳ ይባላል። ከተማ ውስጥ ሆቴል እንዳለውና “120” የሚባል የማፊያ ቡድን እንዳደራጀ፣ የፈለገውን ቢያደርግም ጠያቂ እንደሌለው ነው የተነገረኝ። እራሱ በቪዲዮ የቀረፃቸው የድብደባ ቪዲዮዎችም የሚያሳዩት ይህንኑ ነው።

አንድ ሳይሆን በተለያዩ ቪዲዮዎቹ ካሳዬ አንድ ቤት ውስጥ እያስገባ የሚደበድባቸው ሰዎች ብዙዎቹ በኦሮሚኛ ይማፀኑታል። ያለቅሳሉ፣ ይጮሃሉ፣ እሱ ግን በጭካኔ ይቀጠቅጣቸዋል።

አንዱን ሰውዬ ደግሞ ህዝብ መሃል ነው የሚደበድበው። የአምቦ ከተማ ፖሊስና የከተማው አስተዳደር ይህ ሁሉ ሲፈፀም ምን እየሰራችሁ ነው? 120 የተባለው የማፊያ ቡድንስ ምንድን ነው? ህዝብ መናገር ፈርቶ እንዲህ እስኪሳቀቅ ድረስ አንድ ግለሰብ እንዲህ በአደባባይ ሰው በቪዲዮ እየቀረፀ ሲያሰቃይ እውነት አምቦ ላይ ምን እየተሰራ ነው ያስብላል።

የከተማዋስ ከንቲባ ስለዚህ ሰውዬና ስላደራጀው 120 የሚባል ቡድን ያውቃሉ ወይ? ይሄ ሰው ባስቸኳይ በህግ ጥላ ስር ውሎ ጉዳዩም በፌደራል ደረጃ ካልታየ እንዳየናቸው ቪዲዮዎች ከሆነ ከፍተኛ ጥፋት እንደሚያደርስ ከወዲሁ መናገር ይቻላል። አምቦ ምን እየተሰራ ነው?!💔🙏

via: Natnael Mekonnen

ኮማንደሯ ተገደሉ! የከምባታ ዞን ፖሊስ ባልደረባ የሆኑት ኮማንደር አልማዝ ዮሀንስ በቀን ትላንት ማንነታቸዉ ለጊዜዉ ባልታወቁ በድንገት በተፈጸመባቸው ተኩስ ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
14/04/2026

ኮማንደሯ ተገደሉ!

የከምባታ ዞን ፖሊስ ባልደረባ የሆኑት ኮማንደር አልማዝ ዮሀንስ በቀን ትላንት ማንነታቸዉ ለጊዜዉ ባልታወቁ በድንገት በተፈጸመባቸው ተኩስ ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።

ታገደየቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም "ኢትዮሪካ"ን አስመልክቶ ማክሰኞ  ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም  ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ በይፋ ታግዷል። እንዳረጋገጡት፣ ቴዲ ከተለያዩ ጋዜጠኞች ጋር ...
13/04/2026

ታገደ

የቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም "ኢትዮሪካ"ን አስመልክቶ ማክሰኞ ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ በይፋ ታግዷል። እንዳረጋገጡት፣ ቴዲ ከተለያዩ ጋዜጠኞች ጋር የሚያደርገውን ይህንን መግለጫ በቀጥታ ለማስተላለፍ ከአርትስ ቲቪ (Arts TV) ጋር አስቀድሞ ስምምነት ተፈራርሞ ነበር።

ይሁን እንጂ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የቴሌቭዥን ጣቢያው ይህንን ፕሮግራም እንዳያስተላልፍ ጥብቅ እገዳ በመጣላቸው የቀጥታ ስርጭቱ እንዲቋረጥ ተገዷል። በብዙዎች ዘንድ በናፍቆት የሚጠበቀው የቴዲ አፍሮ "ኢትዮሪካ" አልበም፣ ገና በይፋ ሳይለቀቅ ከወዲሁ በመላው ሀገሪቱ ከፍተኛ ውጥረትና መነጋገሪያ እየፈጠረ ይገኛል።

Address

Any Where
Addis Ababa
291

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አደይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share