Bilen mesfin

Bilen mesfin Ethiopia

ማስታወቂያና ማሳሰቢያ ከዶ/ር ምስጋናው አንዷለምይድረስ ለሁሉም አማራ፣ በተለይም ለጎንደርየዶ/ር ምስጋናው ይህ አቋም የግለሰብ ሳይሆን የብዙዎቻችን መሆኑ ይሰመርበት።ለትውልዱ ኮፒና ፕሪንት እ...
19/04/2026

ማስታወቂያና ማሳሰቢያ ከዶ/ር ምስጋናው አንዷለም

ይድረስ ለሁሉም አማራ፣ በተለይም ለጎንደር

የዶ/ር ምስጋናው ይህ አቋም የግለሰብ ሳይሆን የብዙዎቻችን መሆኑ ይሰመርበት።

ለትውልዱ ኮፒና ፕሪንት እየተደረገ ይሰራጭ!

ጎጃም የክልሉን ስልጣን ጠቅልሎ በያዘበት የአማራ ክልል የጎንደር ፣ ሸዋ እና ወሎ አጃቢነት እስከመቼ ነው?የአማራ ክልል ቢሮ የስልጣን ድልድል ተከታዩን ይመስላል.     ጎጃም.... 38 የቢ...
21/03/2026

ጎጃም የክልሉን ስልጣን ጠቅልሎ በያዘበት የአማራ ክልል የጎንደር ፣ ሸዋ እና ወሎ አጃቢነት እስከመቼ ነው?
የአማራ ክልል ቢሮ የስልጣን ድልድል ተከታዩን ይመስላል.

ጎጃም.... 38 የቢሮ ሀላፊ (53%)
ወሎ..... .16 የቢሮ ሀላፊ (22%)
ጎንደር.... 11 የቢሮ ሀላፊ (15%)
ሽዋ........ 6 የቢሮ ሀላፊ (8%) ድርሻ አላቸው😭😭።
ጎጃም

1. ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ #ጎጃም
2. ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የግብርና ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ድረስ #ጎጃም
3. ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ #ጎጃም
4. ገንዘብ ቢሮ አታላይ #ጎጃም
5. የአባይ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሀላፊ አበባው #ጎጃም
6. የገጠር መንገድ ባለ ስልጣን ቀለሙ #ጎጃም
7. ማዕድን ቢሮ ሀይሌ #ጎጃም
8. ውሃ ቢሮ ዶከተር ዳኝነት #ጎጃም
9. እንሰሳት ሀብት ሀላፊ ዶክተር ጋሻው #ጎጃም
10.ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ጥላሁን #ጎጃም
11. ሚኒሻ ፅ/ቤት አስቻለ #ጎጃም
12. ሲቨልሰርስ ባንችአምላክ #ጎጃም
13. ጠቅላይ ፍርድ ቤት አለምአንተ #ጎጃም
14.ህብር ኮንስትራክሽን መብት #ጎጃም
15. ልህቀት ዲዛይን ቁጥጥር አብረሃም #ጎጃም
16. ምርጥ ዘር ኢንተር ፕራይዝ ጀንበሬ #ጎጃም
17. የፓለቲካ ስርአት ግንባታ ዶክተር መስፍን #ጎጃም
18.የህብረተሰብ ተሳትፎ ወርቁ #ጎጃም
19. ስቴት ዪኒቨርስት ፕሬዝዳት ዶክተር ማተቤ #ጎጃም
20. የከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ሀላፊ ዶክተር ምትኩ #ጎጃም
21. የፖርቲው የሰው ሀይልና ፋይናን ሀላፊ ስመኜው #ጎጃም
22. ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት ዳንኤል #ጎጃም
23. ውሃ ስራዎች ኮርፖሬሽን ዘመነ #ጎጃም
24. አማራ ብረታ ብረት ዘለአለም #ጎጃም
25. ህብረተሰብ ጤና በላይ #ጎጃም
26. ብቃት ማረጋገጫ ባዘዘው #ጎጃም
27. ሰቆጣ ቃል ኪዳን ባዘዘው #ጎጃም
28. የግል ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አዲሴ #ጎጃም
29. ወጣት ሊግ ተስፋሁን #ጎጃም
30. ሴቶች ኢለኔ #ጎጃም
31. ምክር ቤት ፅ/ቤት ሰብለ #ጎጃም
32. ስራ አመራር ምክትል እሱባለው #ጎጃም
33. የርዕሰ መስተዳደሪ ልዩ አማካሪ ይትባረክ #ጎጃም
34. Ag ፊቲንግ ወለላ #ጎጃም
35. አካባቢ ጥበቃ ተስፋሁን #ጎጃም
36. ሰማዕታት አዲስ #ጎጃም
37. ቅርፅና ጥበቃ ባይነሳኝ #ጎጃም
38. የአሚኮ ዋና አማካሪ ግዛቸው #ጎጃም
39. የአሚኮ የህግ አማካሪ አቡዬ #ጎጃም
40. የከተማ ልማት ዋና አማካሪ ሽቤ #ጎጃም
41. የህብረት ስራ ዋና አማካሪ ሀይለልኡል #ጎጃም
42. ግብርና ምርምር ሀላፊ #ጎጃም
43.ፀረ ሙስና ሀብታሙ #ጎጃም
44.የገብያ ማዕከላት ሀላፊ ተዋቸው #ጎጃም
45.ሳይንስና ቴክኖሎጂ የቻለ #ጎጃም

ወሎ

1.ምክል ርዐሰ መስተዳድር ዶክተር አብዱ ወሎ
2. አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ፍስሀ ወሎ
3. ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ዘሪሁን ወሎ
4. አብዱ ከሪም ጤና ቢሮ ወሎ
5. መንገድ ቢሮ ዶክተር ጋሻው ወሎ
6. ፀጥታ ቢሮ ዶከተር,እሸቱ ወሎ
7. ፖሊስ ኮሚሽን ዘለአለም ወሎ
8. ዘመን ኮንስትራክሽን ታደሰ ወሎ
9. አማራ ፓይፕ ወንድወሰን ወሎ
10. አፈ ጉባኤ ፋንቱ ወሎ
11. ምግብ ዋስትና ዳቆንተስፋው ወሎ
12. ስራና ስልጠና ዶከተር ስቡህ ወሎ
13. ወሳኝ ኩነት መአዛ ወሎ
14.ገቢዎች ዶክተር መንገሻ ወሎ
15. ዋሊያ ካፒታል ወንድ አለ ወሎ

ጎንደር

1. ፖርቲ ሀላፊ ይርጋ ጎንደር
2.ምክትል ርዕስተዳድር የአስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ
2. ንግድ ቢሮ ዶክተር ኢብራሂም ጎንደር
3. መሬት ቢሮ ሀላፊ ሲሳይ ጎንደር
4. ሴቶች ህፃናት ብርቱካን ጎንደር
5. ባህል ቱሪዝም መልካሙ ጎንደር
6. ህብረት ስራ ጌትነት ጎንደር
7. ደን ኢንተር ፕራይዝ ቢያድግልኝ ጎንደር
8. ኢንዱስትሪ ፖርኮች ብርሀኑ ጎንደር
9.ከተማ ልማት ዶክተር ሞላ
10. ኮሙኒኬሽን አባይ
11.አሚኮ ስራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ጎንደር

ሸዋ

1. ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር አህመዲን ሸዋ
2.ፕላን ቢሮ ዶከተር ደመቀ ሸዋ
3.ፍትህ ቢሮ ብርሀኑ ሸዋ
4.ኢንቨስትመንት ቢሮ እንድሪስ ሸዋ
5.የርዕሰ መስተዳድሩ የህግ አማካሪ ገረመው ሸዋ
6.ግብርና ቢሮ ደረጀ ሽዋ

የግል አቋም መግለጫ  ስዩም ይዘንጋው ድንቁ ለህዝብ አድርስልኝ ሲል የላከልኝ ነው።  "መንጫጫት ይቻላል ። የመንጋ ጫጫታ ግን ከሣምንት አያልፍም"    ከ2008 እስከ መጋቢት  2010 ዓ.ም...
11/10/2025

የግል አቋም መግለጫ
ስዩም ይዘንጋው ድንቁ ለህዝብ አድርስልኝ ሲል የላከልኝ ነው።

"መንጫጫት ይቻላል ። የመንጋ ጫጫታ ግን ከሣምንት አያልፍም"

ከ2008 እስከ መጋቢት 2010 ዓ.ም ከሕወሃት ጋር በነበረው ትግል በወቅቱ በነበረው የትግል ስልት የራሴን አስተዋጽኦ አበርክቻለሁ። በኋላም አብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ሲመጣ ለውጥ ሲባል እንደ ማንኛውም ሰው ለአብይ አሕመድ አጨብጭቤያለሁ። ለውጥ ወደ ነውጥ ተጀመረ ።ሕወሃትን አምርሬ ስጠላ ስለነበረ ልታገሰው በማለት ከአሁን አሁን አብይ አሕመድ ያሻሽላል እያልኩ እስከ 2013 ታገስኩት። በመጨረሻም አማራው በወለጋ በመተከል መገ-ደል መፈናቀል ሲባባስ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ፋኖ ነኝ አማራ ዳግም በሕወሀት አይገዛም በኦነግ ሸኔ አይፈናቀልም ብየ በግሌ ስታገል ቆይቻለሁ። በዚህም የተነሳ ብልጽግና እንደ ሌላው የአማራ ሕዝብ በእኔም ግፍ ፈጽሞብኛል።
በኋላም አብዮቱ ሲፈነዳ ከቤቴ ወጥቻለሁ። እስከ ዛሬም ከፋኖ ጋር ሆኘ ጭቆናን ስቃወም ስታገል ቆይቻለሁ።
አሁን ግን

በአብይ ዘመን ኦነግ ሸኔ አማራውን እያገተ አምስት መቶ ሺ ፣ አንድ ሚሊየን ብር አማራውን እየጠየቀ ነው ብለን በእልህ ወጥተን ከትግሉ ላይም ከኦነግ በባሰ ከምስኪኑ ህዝብ ሰበብ እየተፈለገለት ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ እንደምትባል ሁሉ ሊዘርፉት ያሰቡትን ምስኪን "ባንዳ" የሚል ቅጽል እየሰጡ ሦስት መቶ ሺ -፣ አምስት መቶ ሺ ፣ 2 ሚሊየን ብር ገንዘብ ክፈሉ እየተባሉ በርካታ ሰዎች ሲሰቃዩ በተደጋጋሚ ስላየሁ ከኦነግ ሸኔ በመባሳችን ።
ኦነግ ሸኔ - አማራውን በወለጋ ምድር ገደ-_ለ- ው ብለን ትግል ጀምረን ነጻ እናወጣሃለን እንታገልልሃለን የምንለውን ሕዝብ ስናሰቃይና ሲገ--_ደል በማየቴ ። ትግሉ በሚደረግበት በሁሉም አካባቢ ግፍ መፈጸሙን ባውቅም እንኳ እኔ ካየኋቸውና ከዘገነኑኝ ሕመም ከሆኑኝ ግፎች መካከል ለአብነት ጥቂቶቹን ፦

በወለጋ - በመተከል የአማራ እናቶች ሆድ እየተቀደደ ጽንስ ወጣ ብለን ትግል እንዳልጀመርን ሁሉ
1ኛ፦ ዋሸራ በእናቶች ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ በጥይት ድብ-_ደባ ።ይህም በዝምታ መታለፉ
2ኛ፦ ዘማ ባለሆቴል ንጹህ ግለሰብ ግድያ_ ፋኖው ሰራተኛዋን ይዣት ካላደርኩ ካልወሰድኩሽ ሲላት እምቢ ስትል ባለሆቴሉ ተዋት ያለፍላጎቷ አትውሰዳት በማለቱ ብቻ መገ- ደሉ።

3 ኛ፦ ሕወሃት -ኢሕአዴግ በወንጀል ምርመራ ወቅት ቶርች አደረገ - ሀይላንድ አንጠለጠለ- እያልን ስንታገል ስንቃወም እንዳልነበረ ሁሉ በምርመራ ወቅት የሚፈጸም ኢሰብአዊ የሆነ ድርጊት በማየቴ ከበርካቶች ለአብነት ያክል___

3.1 ፦ ቢቡኝ ወረዳ ገናመምቻ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ምስኪን አርሶአደሮች አረፋ ደብተራ ተወስደው እሳት በፔስታል እየተንጠፈጠፈ መቃጠ-----ላቸው።


3.2 ከቋሪት ወደ አረፋ ለለቅሶ መጥቶ የነበረ አርሶአደር መረጃ ነህ ጸጉረ ልውጥ ነህ ተብሎ ግንባራ ከተባለ ወንዝ ውስጥ አስገብተው ውሀ እየነከሩ በጭካኔ ተናገር እያሉ ሲገርፉ ቆይተው በመጨረሻም በጥ-ይ-ት ገድ-ለው ውሀ በላው እንዲባል ወደ ግንባራ ወንዝ ወርውረው አስከሬኑን እንኳ በወንዝ ማስወሰዳቸው የአዕምሮ ሕመም ስለሆነኝ።

በእኔ ዕድሜ ካየኋቸው አገዛዞች በእኔ አካባቢ ኢህአዴግም ብልጽግናም ያልፈጸመው አዲስ የአውሬነት መንፈስ ባሕሪ ስላየሁና ከወጣሁበት ትግል አማራን ከ ማዳን -ተቃራኒ ስለሆነብኝ ። ከላይ የጠቀስኳቸውና ጋር የሚመሳሰሉ በርካታ አረመኔያዊ ባሕሪ ከጭቆና ነፃ እናወጣሃለን በሚባለው ሕዝብ ላይ ታይቶ የማይታወቅ ግፍና በደል ሲፈጸም እያየሁ ሕሊናየ መቋቋም ስላቃተው።

ሌላው
ብልጽግና ጨቆነን እነ ክርስቲያን ታደለን እነ መስከረም አበራን በሐሳብ ስለሞገቱ ለምን ይታሰራሉ ?? ብለን ትግል ወጥተን ሳለ የሚሰርቅ የሚያጭበረብር ፋኖ መታሰር ሲገባው በሐሳብ የሚሞግቱ ፤ የተለየ ሐሳብ አላችሁ - የአፋሓድ ተላላኪ ናችሁ የእስክንድር ናችሁ - " እየተባሉ በመጠላለፍ ፍረጃ እየተሰጣቸው ፋኖዎች በአስከፊ ሁኔታ ከቂልንጦ ከአዋሽ አርባ የከፋ ድቅድቅ ጨለማ ክፍል ውስጥ ከአመት በላይ ታስረው እየተገረፉ በማየቴ ።
ያጠፋ በአግባቡ ሊታረም ይችላል። ከዚህም መካከል ምንም ጥፋት ቢኖር እንኳ በመጠኑ ለትንሽ ጊዜ አርሞ ማስወጣት እየተቻለ ጎጃም የትጥቅ ትግሉ በይፋ ሳይጀምር ቀድማ በወሎ በኩል በ2014 ዓ.ም ጀምራ የትጥቅ ትግል የጀመረችዋ ታጋይ አስካል ደምሌ አጅግ አስከፊ በሚባል ቤት ተዘግቶባት ጨለማ ቤት ዓመት እየማቀቀች መሆኑን በወርኃ ሐምሌ ተረድቼ ስለሰቀጠጠኝ ወርኃ ሐምሌን በሕመም መጨረሴ ።

እነ ክርስቲያን ታደለ መስከረም አበራ በሐሳብ አመለካከታቸው ለምን በብልጽግና ይታሰራሉ ብሎ የሚጮህ የነጻነት ታጋይ
ደግሞም ኢሕአዴግና ብልጽግናን ኢሰብአዊ የእስረኛ አያያዝ ይፈጽማሉ፣ የሐሳብ ነጻነት ይከበር የመናገርና የመፃፍ መብት ይከበር እያልን ስንታገል ከቆየነው በተቃራኒ በመሆኑ።በሐሳብ ልዩነት መታፈኗ !!!!! ታፍናም በአግባቡ አለመታሰሯ ።ታስራም በቶሎ መፍትሔ አለማግኘቷ ። "ያን ሲያማ ለእኔ ብለህ ስማ " በመሆኑ ለሴቷ እንዲህ የግፍ እስር የጨከነ የነጻነት ታጋይድርጅት ለሕዝብ ነጻነት እንደማይበጅ በመረዳቴ።

ወደ ፊት እንኳ አራት ኪሎ ለመግባት ቢቀና ስንታገልለት የነበረውን " ነጻነት" ለሕዝብ እንደማንሰጥ። አሁን ላይ ቶሎሳ ወይ ጅረኛ የተባለ ኦሮሞ በብልጽግና በኩል ከጨቆነኝ ቀጣይ አለማየሁ ወይ ከበደ የተባለ ፋኖ እንደሚጨቁነኝ የመደብ ጭቆና እንደሚቀጥል እንጂ መሠረታዊ የአማራ መብት እንደማይከበር ስለተረዳሁ።
አሁን ላይ ከተማውን ብልጽግና ሲያስተዳድር _ አብዛኛውን ገጠሩን ደግሞ ፋኖ ያስተዳድራል ። ነገርግን አሁን ላይ በሕዝብ ጭቆና ደረጃ ፋኖ ከብልጽግና አቻ በሚባልበት ደረጃ ላይ እንዳለ ስለተረዳሁ

👉 ከሕዝብና ከዲያስፖራው ገንዘብ እየተሰበሰበ ለፋኖ አመራሮች አዋሳና ድሬደዋ ቤት መግዣ ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ደግሞ ለኢንቨስትመንት መዋሉን ስለተረዳሁ።
በትግል ስም የሰበሰቡት ገንዘብ እያሳሳቸው የፋኖ ታጋዮች በየጊዜው ከትግሉ እየኮበለሉ ወደ አዋሳና ድሬድዋ አዲስአበባ እየገቡ መሆኑ።
በተቃራኒው በትግሉ የቆሰሉ፣ እግራቸውን ያጡ። ሁለት ዐይናቸውን ያጡ ታጋዮች እያሉ ለሕክምና መሰጠት ሲገባቸው ከትግሉ በፊት አረቂ መጠጫ አስር ብር እንኳ ያልነበራቸው ዛሬ የፋኖ አመራር የሚባለው ሚሊየነር - ኢንቬስተር መሆኑን ስለተረዳሁ።
የፋኖ አመራር በወር ከ30,000(ሰላሳ ሺ ) እስከ 50,000 (አምሳ ሺ ) ብር እንደሚያገኝ በማየቴ። ይህም በጎጥ በወረዳ ሐብት ለማካበት ሲሉ መሠረታዊ ለውጥ አንድነት የማይፈልጉ ፣ በከተሞች በዘመድ አዝማድ የጀመሯቸው ፎቆች እስከሚጠናቀቁ ማሰሪያ በትግል ስም ገንዘብ ለመሰብሰብ ትግሉ ቢራዘም የሚወዱ ፣ አንድነት ተፋጥኖ የሕዝብ ጭቆና በቶሎ እንዲመጣ የማይገዳቸው እንዳሉ ስለተረዳሁ

አብዛኛው የፋኖ አመራር ከዲያስፖራም ከገበሬ መዋጮም በሚያገኘው ገንዘብ ቤተሰቦቹን ከተማ አውጥቶ እያኖረ የምስኪኑ ፋኖ ቤተሰቦች በብልጽግና የሚታሰሩበት የሚሰቃዩበት። በተየያዘም የፋኖ አመራር ቤተሰቦቹን ከተማ ልኮ እያስተማረ የአርሶአደር ልጆች እንዳይማሩ ትምህርት መከልከሉን ስላየሁ።

👉 አማራ ባለመደራጀቱ ተበደለ ብለን አማራውን አማራ ልናደርግ ፣ አማራ ነን አማራን ከጭቆና ነፃ እናውጣ ብለን "የሕልውና ትግል " በሚል ትግሉ በሕዝባዊነት ተጀምሮ ትግሉ ወደ ፖለቲካ ሥልጣን ሽኩቻ የቁጥቋጦ ሥልጣን ጥቅምና የግለሰብ ዝና ከአማራነት በልጦብን በአውራጃ መዘፈቃችንና በጫካ ሥልጣን አማራው ከአማራነት ዝቅ ብሎ ወደ ጎጃሜነት ፣ ጎንደሬነት እየተገፋ መሆኑን በመረዳቴ ። ይህም ብአዴን እንኳ አንድ አድርጎት የቆየውን አማራ ----- ፋኖ ከብአዴን በማነስ አንድ አማራ ብሎ ትግል ጀምሮ አሁን ላይ ግን ጎጃሜ ጎንደሬ ማንነት እንዲይዝ እየተገደደ እንደሆነ በመረዳቴ ።
የናይጀሪያው ፕሬዘዳንት በአንድ ወቅት ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር ሲወያዩ መለስ ዜናዊ ለናይጄሪያው አቻቸው " የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እየተጣሉብኝ ነው " ይሏቸዋል ። የናይጀሪያው አቻቸውም " አሁን ተጣልታችሁ ሙታችሁ ነው ወይ አሁንማ ድህነት ላይ ናችሁ ምኑ ያጣላችኋል ? - ገና ኢትዮጵያ እያደገች ስትመጣ በኋላ ነው በሐብት የምትጣሉ " አሏቸው ይባላል። በትንሿ የቁጥቋጦ ሥልጣን ይገባኛል ጫካ ሆነው እንዲህ በሥልጣን ሽኩታ አማራውን አንድ ያላደረጉ ያልተማመኑ የሥልጣን ጥማተኞች ፥ ዕድል ቀንቷቸው አራት ኪሎ ቢገቡ እንኳ አማራውን በአውራጃ ከፋፍለው እንደሚያታኩሱት ከወዲሁ በመረዳቴ ።
በትግል የሚመጣ ክፍፍል አንድ ኮርያን ከሁለት የከፈለ አንድ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ኤርትራና ትግራይን ለሁለት የከፈለ እንደሆነ ስለተረዳሁ ። ትግሉም ቀጥታ ጠላታችን ከምንለው ወደ ብልጽግና ሳይሆን አፋጎ_ አፍሃድ- አፋብኃ እየተባባለ የእርስ በርስ የጎንዮሽ ትግል ስድድብ ሲሆን በማየቴ ።

👉ትግሉ ሕዝባዊ ትግል ነው። ነገር ግን ፖለቲካ ፓርቲ በማስመሰል ጥቂት ግለሰቦች አባልም ሕዝብም ሳያማክሩ ከታሪካዊ ጠላታችንና የትግራይ ሕዝብ ሳይቀር አሁን ላይ እየተጸየፋት ያለውን ከወያኔ ጋር ያላቻ ጋብቻ ምስጢራዊ ግንኙነት መፍጠር። ከጎንደር ከጎጃም ከሸዋ ከወሎ ፋኖ መጀመሪያ እርስበርሱ አንድነት ሳይፈጥር ግንኙነቱ አልፎ ከጥንተ ጠላታችን ወያኔ ጋር መሆኑን ስለተረዳሁ። ይህም የማይሳካ ሕወሃት የሚፈልግ ወልቃይትን እኛ ትግል የወጣነው ከጭቆና በተጨማሪ ወልቃይትን ራያን ርስት ለማስከበር በመሆኑ ፋኖ ከወያኔ ጋር የማይገጣጠም የማይሳካ ግንኙነት መሆኑን ስለተረዳሁ። ሕወሓት ከምሁር እስከ ጎጃም ገበሬ ያልበደለችው ሰው ስለሌለ ሕዝብና ታጋዩን ሳያማክሩ በሕዝባዊ ትግል ስም ከሕወሃት ጋር ግንኙነት እንዳለ በመረዳቴ። በዚህ ሰበብ የወልቃይት ጉዳይም ቸላ እየተባለ ስለሆነ የወልቃይት የአማራ ርስትነት ጉዳይም የማያወላውል አቋም ስላለኝ።

👉 በትግሉ በርካታ መስዋዕትነት ተከፍሏል ለእውነት የወጡት ሐቀኞች ጓዶቼ አለኝታዎቼ ተሰውተውብኛል። ለጥቅም ለሌብነት - አማራ ነፃ ይውጣ ሳይሆን ለሥልጣን ለመንገስ የሚቋምጠውና ከዲያስፖራ እና ገበሬ መዋጮ በሚሰበሰብ ገንዘብ እስከ 30 አጃቢ ቀጥሮ በምስኪኑ አርሶአደር መንደር ውስጥ እየታጀበ የሚኖር ፣ ሌላው የቀረው አብዛኛው ታጋይ ለምን እንደሚታገል የማያውቅ ፥ ሚሊሻና ፖሊስ ደበደበኝ ገረፈኝ ብሎ ወደ ጫካ ወጥቶ እሱም በተመሳሳይ እንደ ሚሊሻ ሕዝብ ሲገርፍ ሲያሰቃይ የሚውል ፋኖ አለ። ከትግሉ ውስጥ በጣት የሚቆጠሩ ጥቂት እውነተኞች ቤትና ትዳራቸውን በትነው ሥራቸውን ለቀው ለሥልጣን ለጥቅም ያልወጡ ቢኖሩም በትግል ስም ገንዘብ አካብተው አንድ ሻምበል አጃቢና 30 አክቲቪስት በቀጠሩ የፋኖ ካድሬዎች ስለሚኮረኮሙ አድርባይነት፣ አስመስሎ መኖርን መርጠዋል። ግፍ ሲፈጸም አርሶአደሮች ፣ መምህራን እየታሰሩ ሚሊየን ብር ሲጠየቁ ሲገረ- ፉም ዝም የሚሉ ናቸው ።(ከአድርባዮች መካከል አንዱ እኔ ነበርኩ።) በዚህ ምክንያት ሀይ የሚል የሚገስጽ ስለጠፋ ፋኖ በሕዝብ ላይ የሚፈጽማቸው በደሎች በዙ።
ሕዝብ እየተበደለ " አብዮት ነው መጨከን አለብን ዝም በሉ " በማለት ለሕዝብ ብሎ የወጣ ፋኖ ድርጅትን ከሕዝብ በማስበለጥ ድርጅት ይጠለሻል እያሉ ሕዝብ ሲበደል ዝም ብሎ ማየት፣ በአጠቃላይ ነፃ እናወጣሃለን በተባለው ሕዝብ ላይ ፋኖ የሚጽማቸው ጆሮን ጭው የሚያደርጉ በደሎችና ግፎችን ስሰማ ስመለከት ትዕግስቱን ስጠኝ ፣ ልቦና ስጠኝ እያልኩ ፈጣሪየን እግዚአብሔርን እየለመንኩ ዝም ብየ ቆይቻለሁ። አሁን ላይ ግን በሕዝብ ላይ የሚፈጸሙ በደሎች እየተደጋገሙ ስለበዙ ልቦናየ ሊቋቋማቸው ባለመቻሌ፣ ግፍ ሲፈጸም ሰምቶና ዓይቶ የመቻል፣ ዝም የማለት አቅሜን ስለጨረስኩ ዝምታ አፍኖ ጤና ስለነሳኝ ፤ ቀጣይም ቢሆን ድርጅት ነው ዝም በል መባሌ ስለማይቀር ድርጅት ነው ዝም በል እየተባልኩ የመጻፍና የመናገር መብቴንም ስለተገደብኩ ስንናገርም " አንጃ" እየተባለ ሌላ ፍረጃ የእስክንድ ደጋፊ ነህ ፣ አፍሃድ ነህ፣ አፋብሀ ወዘተ መባባሉ ፍረጃ ስለቀጠለ ፣ ከዚህ በፊት በትግሉ ሚሊየነር የሆኑ ሌቦችን በ2016 ዓ.ም በመቃወሜ እና በ 2017 ዓ.ም የዋሸራ ግፍ መጻሚዎችን በማውገዜ ሌላ ሰበባዊ ወንጀል ተፈልጎልኝ ሁለቴ ይታሰርና ይረ-_ሸን ተብዬ ሁለቴ ከሞት ተርፌያለሁ።በገባኝ ልክ ታግያለሁ ፣ አሁን ላይ ትግሉ እየገባኝ ስላልሆነ ሳይገባኝ መታገል ማደናገር ስለሆነ ብሎም የወጣሁ ለሕዝብ እንጂ ለድርጅት ስላልሆነ ከሕዝብ ድርጅት ስለማይበልጥብኝ ከላይ የጠቀስኳቸው መሰረታዊ ችግሮች ይቀረፋሉ ስል እየተባባሱ ስለመጡ ከድርጅት ራሴን በማግለል ከቤቴ በገሐድ ለትግል እንደወጣሁ ሁሉ ፣ አሁንም በገሐድ ወደ ቤቴ በመመለስ የዝምታ ዝምታ ወደ ቤቴ ተመልሼ ከቤቴ ዝም ለማለት ወስኛለሁ።

ነሐሴ 17 -2017 ዓ.ም
አስተርዕዮ

መንጫጫት ይቻላል ። የመንጋ ጫጫታ ግን ከሣምንት አያልፍም። ደሕና ሁኑ!!!!!!!!
Ayalew Menber

የባህር ዳሩ  #ከአልማ እስከ  #ዋተርፍሮንት ሆቴል ያለው  #መንገድ ግንባታ እና የሚዲያ ዘመቻ ሰለባው  #የሬማ ኮንስትራክንሽን ጉዳይ=================(ሰሞኑን የሰነበትኩት ባህር ...
27/09/2025

የባህር ዳሩ #ከአልማ እስከ #ዋተርፍሮንት ሆቴል ያለው #መንገድ ግንባታ እና የሚዲያ ዘመቻ ሰለባው #የሬማ ኮንስትራክንሽን ጉዳይ
=================

(ሰሞኑን የሰነበትኩት ባህር ዳር ከተማ ሰነድ (ማስረጃ) በመጎርጎር ነው።አይን ገላጭ ማስረጃ አግኝቻለሁና በጥሞና ተከታተሉት።ትዕግስት ከሌላችሁ አትጀምሩት)

የሆነ ጥቆማ ሲመጣልኝ ብዙ ጊዜ የማምናቸው የምላቸው የተለያዩ ሰዎች ጋር መረጃውን ለማረጋገጥ እሞክራለሁ።በዚህ ሁለት ሶስት ወር ግን እና #የትምህርት ጉዳይ ዋና አጀንዳዎቸ ስለነበሩ ከዚህ አጀንዳ ውጭ የሆኑ አንዳንዶቹን ጥቆማዎች ብዙ ርቀት ተጉዠ ለማጣራት ጊዜ አላገኘሁም ነበር።

ባለፈው "ጎንደር ትሞሸር" የተባለ ሰሞን መሳይ መኮነን ለመስማት የሚዘገንን ነገር ዘግቦ አንዳንድ ወዳጆቸ በግል ደውለው "ይህ ግልፅ ጥላቻ ነው" በማለት እስከመሰዳደብ ደርሰው ነበር። በቅርቡ ደግሞ ሀብታሙ አያሌው በተከታታይ (ሁለት ጊዜ) ፕሮግራም የሰራባቸውን ጉዳዮች ምክንያቱ ምን ይሆን? የመረጃው ተዓማኒነትስ ምን ይሆን በሚል ድጋሚ ለማጠራት ሞከርኩኝ።የሆነ ነገር ሲሸተኝ ሱስ አለብኝ።መረጃ ማነፍነፍ እወዳለሁ።

አንደኛው ጉዳይ ለእኔም በተሳሳተ መንገድ ደርሶኝ በደንብ ባይሆንም በስሱ ፅፌው ነበር ይመስለኛል😀። አፉ በሉኝ።

በእኔ በኩል የሚመጡ ጥቆማዎችን ብዙውን ጊዜ ግራና ቀኝ ካላጣራሁ አየር ላይ አላውላቸም።በዚህ ሁሉት ወር ግን ህዝብን ለመጥቀም በሚመስል መልኩ ነገር ግን ግለሰቦችን ለማጥቃት የሚውሉ ሁለት ጥቆማዎች ደርሰውኛል። በተጠናከረ መልኩ ባይሆንም እኔም በአየር ላይ አውያቸዋለሁ።ይህንን ሳስብ አንድ የብልፅግና ቅርብ ሰው ከሰሞኑ "ተደጋጋሚ አንተን ለማሳሳሳት ሞክረን አልተሳካልንም ነበር።ክፉ ሰው ነህ ዛሬ ግን አገኘንህ" ያለኝን አልዘነጋውም።እንዲህ ያሉ አካሄዶች የተሳሳተ መረጃ ለግለሰቡ በመስጠት ተዓማኒነቲንን ለመቀነስ የሚደረግ ክፋ ተግባር ነው።ግን ብዙ ጊዜ ጠንቃቃ ነኝ።
እኔ እዚህ ሚዲያ ላይ የምቆየው ማንም ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት አይደለም።የግል ፀበኛ የለኝም።ህዝብ እንዳይበደል፣ የህዝብ ሀብት እንዳይመዘበር፣ ባለስልጣናት በስልጣን እንዳይባልጉ ብቻ ነው ፍላጎቴ።ይህንን ፍላጎቴን ተጠቅመው የግል ቂመኛቸውን ለማጥቃት ሲጠቀሙብኝ እናደዳለሁ።ሰዎች ሆን ብለው ግለሰቦችን ለማጥቃት
=>( አልያም
=> ወይም
=> ወዘተ) ብዙ ተከታይ አላቸው ወይም ህዝብ ይሰማቸዋል የሚባሉትን ይጠቀማሉ። በዚህ መልኩ ሌላላውን ለማጥቂያ እንደተጠቀሙብኝ ሳውቅ በእውነቱ ሽንፈት ነው የሚሰማኝ።

===================

ወደ አጀንዳየ (ሬማ ኮንስትራክሽን ጉዳይ) ልመለስና
የሰሞኑ የሬማ ኮንስትራክሽን ዘመቻም ብዙ ርቀት ተጉዠ ያረጋገጥኩት እውነታ ቢኖር ምንጩ ከላይ ከጠቀስኩት ሶስት ምክንያት እንደማይዘል ነው።

ደረቁን መረጃ እንደወረደ ላጋራችሁና እናንተ ፍረዱ:-

የከተሞች የኮሪደር ልማት ሲታሰብ ባህር ዳር አንዷ ናት።ከባህር ዳር ደግሞ ለረጀም ዐመታት ሲታቀድ የቆየና ያልተሰራ ከድብ አንበሳ ዋተር ፍሮት (ፓፒረስ) የሚደርሰው 800ሜትር ርዝመት ያለው የባለ 40ሜ ዘመናዊ መንገድ ግንባታ ይገኝበታል።ከተማው አጋጣሚውን ተጠቅሞ ያንን መንገድ ማሰራት ፈልገና ግልፅ ጨረታ አወጣ። (ቆፍሬ የገኘሁትን የተያያዘውን ማስረጃ ተመልከቱ)። #አምስት ተጫራቾች ቀረቡ።

የተጫራቾች ዝርዝር እና ያቀረቡት ዋጋ

1). አሚጊት .....1.95 ቢሊዮን ብር አቀረበ
2).መለሰ........ 1.91 ቢሊዮን ብር አቀረበ
3).ጥበብ....... 1.85 ቢሊዮን ብር አቀረበ
4). በረከት..... 1.80 ቢሊዮን ብር አቀረበ
5). ሬማ..........1.68 ቢሊዮን ብር አቀረበ

መንግስት ዝቅተኛውን (ወጭ ይቆጥብልኛል ያለውን) ሬማ ኮንስትራክሽንን መረጠ እና አሸናፊውም በአደባባይ ተለጠፈ።ውሳኔው ላይ "አማካሪው ያቀረበው 1.3 ቢሊዮን ስለሆነ ዝቅተኛ ወጭ ያቀረበው የጨረታው አሸናፊ (ሬማ) አሸናፊነቱ ተገልፆ መጠነኛ ማሻሻያ እንዲያደርግ ድርድር ቢደረግ ይላል በ03/08/2017 ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ።በ15/09/2017 ዓ. ም የመንገድ ግንባታው ውል ማሻሻያ በተመለከተ ደባዳቤ ተፃፈና ስምምነቱ በ1.5ቢሊዮን ፀደቀ ስምምነቱ ፀደቀ።

ከዚህን ጊዜ በኃላ በጨረታው ዝቅተኛ መጠን ያቀረበውና በ1.68 ቢሊዮን ብር አሸናፊው ሬማ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተደራድሮ በ1.5 ቢሊዮን ብር ስራውን ሊሰራ ቦታውን ተረከበ።ስራውንም እየሰራ እንደሆነ ከቦታው አረጋግጫለሁ።
በሙያዊ ግምገማ ምን ያህል ነው የሚለውን ለባለሙያዎች ልተወውና አሁን ባለው ሁኔታ የግንባታው 70% በሁለት ወር ብቻ ማጠናቀቅ ተችሏል ብለውኛል።30% ገንዘቡን እንኳን ሙሉውን አልወሰደም።በሚዲያ ግን ያለጨረታ እንደተሰጠው፣ ቅድሚያ ክፍያ እንደወሰደ፣ 2.2 ቢሊዮን ብር ለእርሱ ተብሎ እንደተሰጠው ተዘመተ።

ዘመቻው ግን ፍፁም ውሸት ነበር።የእኔ ጥያቄ በዚህ ፍጥነት እና ጥራት እንዴት ሊሰራው ቻለ? የሚለው ነበር።ያገኘሁት ምላሽ ኮንትራክተሩ ልምድ ስላለውና ሌሎች ፕሮጀክቶች ስላሉት ሙሉ የግንባታ ማሽንና እቃው ከአአ አስመጥቶ እያሰራው ስለሆነ ነው የሚል ነው።ፕሮጀክቱ ልዩ ክትትል ስለሚሻም ኬንትራክተሩ ሙሉ አቅሙን እየተጠቀመ ነው።

አሁን ዋናው ጥያቄ የጨረታ ሂደቱ ህጋዊነት አይደለም።ህጋዊ ሂደቱን ጠብቆ የተከናወነ ነው።እኔ ጋር ቀርቦልኝ የነበረው "የተጋነነ ዋጋ ነው" የሚል ነበር።ይህንን በተመለከተ ሁለት ማስረጃ አግኝቻለሁ።አንደኛው የግንባታው ዋጋ አአ ላይ ከሚሰራበት ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ሁለተኛው ደግሞ መንገዱ በአማራ ክልል እስካሁን ያልተሰራና ለሙከራ በሚል የውሃ፣ የመብራት እና የቴሌ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ሁሉም ከመሬት በታች የሚቀበሩ መሆናቸውና ዘመናዊ ማፋሰሻ እንዲሰራለት ስለተደረገ እንደማንኛውም አይነት መንገድ ግንባትታ አለመሆኑን ነው።
በዚህ ስራም የባህር ዳር ከተማ በክልሉ ተሸላሚ እንዲሆን አስችሎታል።

ሬማ ኮንስትራክሽን ላይ የተደረገው የውሸት ዘመቻ እና ስም ማጥፋት ትክክል አይደለም፣ አልነበረም! ግልፅ ጥላቻ፣ ግልፅ ቅናት እና ሌላን አካል ለማጥቃት የተደረገ ዘመቻ ነው።

ከተማ አስተዳደሩ አካባቢ ባደረግኩት የመረጃ ማነፍነፍ ስራ ያረጋገጥኩት

=>ጨረታው ህጋዊ ሂደትን የተከተለ ነው።
=>እንኳንስ ቀድሞ ሊወስድ ግንባታው 70% ደርሶ እንኳን እስካሁን የቅድሚያ ክፍያውን 30% ሙሉውን አልወሰደም።
=>ፈቃዱና ውሉ የተሰጠውም ለማጥቃት በተጠቀሰው ግለሰብ ሳይሆን በሌሎች ነው። (ሁሉም ማስረጃዎች እጀ ላይ አሉ)።ለተዓማኒነት የጨረታውን ብቻ አያይዠዋለሁም።

እንዲያውም ኮንትራክተሩ ለህዝብ የሚያስብ መሆኑን የምታዩት ካሸነፈበትም 180ሚ ብር ቀንሷል። እየሰራ ያለውም ለከተማችን የመጀመሪያ የሆነውን መንገድ ነው።ኮንትራክተሩ የቅድሚ ክፍያ (advance 30% ) ሙሉ ገንዘቡን ባልወሰደበት ሁኔታ የመንገዱን ግንባታ 70% ካደረሰ ይህንን ጥሩ ስራ ካላበረታታን ማንን ልናበረታታ ነው? ምን ሲሰሩ ልናበረታታ ነው? እንደ ርብ ግድብ 17 ዓመት፣ እንደ አዘዞ መንገድ 12 ዓመት ሲያጓትቱት ነው በርቱ ማለት ያለብን?

እኔ ይህንን መሰል ኮንትራክተር ባገኘው እሸልመዋለሁ እንጅ አልዘምትበትም።በእውነቱ ትችላለህ! በርታ!!አገራችን እንደዚህ ታታሪ ሰው እንጅ ታታሪዎችን ጠልፈው የሚጥሉ አጭበርባሪዎች አያስፈልጓትም! የምታውቁት ምስጋናየን አድርሱልኝ!!

የተሳሳታችሁም ከስህተታችሁ ታረሙ!

እውነታው ይሆኖ ሳለ ታድያ ዘመቻው ምክንያቱና ዓላማው ምንድን ነው? ምንጩስ ማን ነው የሚለውን ለእናንተ ልተወው።

የእኔ ዓላማ እውነትን መግለጥ ነው።ስለ #ቄራውም በቀጣይ በማስረጃ እመለስበታለሁ።በጥላቻና በተንኮል የአማራን ባለሀብቶች ከገበያ ማውጣት መቆም አለበት።

(ማሳሰቢያ:-
እነ ሀብታሙ አያሌው እና መሳይ መኮነንን በመጠቀም የሆኑ አካላትን ለማጥቃት አቅዶ እየሰራ የነበረና ያለ አደገኛ ቡድን መኖሩን አስታውሱ።ይህ ቡድን እጀ ረጅም ነው።በትግል ስም ግን የትግል ቀበኛ ነው።በህዝብ ስም ይምላል።ግን ህዝብ ያማርራል)

Menber

10/09/2025

2017 ዓ.ም አልቀ የት ነህ በሉት ዘሜን 😂😁😁

  ‼️ወንድም እባክህ ማዳን እንኳን ባይቻል ድምፅ መሆን ግፉን ለወገን ማሳወቅ ኅሊና ያለው ሰው ግዴታ ነው ብዬ አምናለሁ። ደምቢያ አብሶ ሰቀልት ወንድ ልጅ የት አለ። የሚገርምህ ትናንት ማክ...
03/09/2025

‼️

ወንድም እባክህ ማዳን እንኳን ባይቻል ድምፅ መሆን ግፉን ለወገን ማሳወቅ ኅሊና ያለው ሰው ግዴታ ነው ብዬ አምናለሁ። ደምቢያ አብሶ ሰቀልት ወንድ ልጅ የት አለ። የሚገርምህ ትናንት ማክሰኞ ለገበያ ጨው በርበሬ ለመግዛት የመጡትን ገበሬዎች በአደባባይ ሲረሽኑ ሲደበድቡ ዋሉ። ሴቶች ተገደው እየተደፈሩ ነው ።

ወንድም ቢያንስ ያደግህበትን ማኅበረሰብ መከራ በመዘገብ ልትረዳን ይገባል። እናድናለን ያሉት ተቧድነው ይገዳደላሉ እናንተም በአንዱ ደጋፊነት ተጠምዳችሁ መሀል ላይ ጠላት ሕዝቡን ድምፅ አልባ ጨረሰው።

ሁለተኛ ጎንደር ላይ የቅማንት ኮሚቴዎች መሪ የነበሩት ጨቡዴና እሄነው አንድ በላይነው ከሚባል ከጎጃም የመጣ ጋር ቅንጅት ፈጥረው የጎንደርን ክፍለ ከተማ ተከፋፍለው በየቀኑ ሌሊት እያንኳኩ ይገድላሉ። አንዱ ምን አለ መሰለህ አዘዞ ሁለት ሰዎች ብቻ ቀርተውኛል አለ። በተለይ አዘዞ 18, ገንፎ ቁጭ ያልተገደለ ወጣት ያልተሰወረ ባለሀብት የለም። ለማን እንናገር።

አስፈላጊ ከሆነ የጅምላ መቃብር የሚፈጸምባቸውን ማክሰኝት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ፣ ጎንደር አየር ማረፊያና መከላከያ ካምፕ ሰራባ የወታደር ካምፕ ነጋዴ ባህር የወታደር ካምፕ። በእውነቱ እያለቀስኩ ነው የጻፍኩልህ። ወገኔ ወጣቱ ድምፅ አልባ የፍጥኝ ታስሮ ተረሽኖ አለቀ። አስፈላጊውን መረጃ ልሰጥህ እችላለሁ ።

በጎንደር አማራውን minority ለማድረግ ወንድ የሚባል እንዳይኖር በማሰር፣ በማፈን በመረሸን ጎንደር የአማራ የደም ምድር እያደረጉት ነው ።
@ገብረማሪያም

መምህር ታደገ ይሁኔ በራሱ ድርጅት አፋጎ  መታፈኑ ተሰማ‼️----------------------------------------------------------------------የአንድነት ፈላጊ ነን...
30/08/2025

መምህር ታደገ ይሁኔ በራሱ ድርጅት አፋጎ መታፈኑ ተሰማ‼️
----------------------------------------------------------------------
የአንድነት ፈላጊ ነን የሚሉ እና ከወንድሞቻችን ጋር የጎንዮሽ ትግል አናደርግም ሲሉ የቆዩት የአፋጎ የክፍለጦርና የብርጌድ አመራሮች በአፋጎ የላይኛው አመራር ወከባ እና እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑ ከተሰማ ሰነባብቷል።

ከጎንዮሽ መገዳደል ወጥተን ከወንድሞቻችን ጋር ማበር ለእኛም እንደ ታጋይ ለጎጃም ሕዝብም የሚጠቅመው እሱ ነው። ስለምን በሸዋ፣ በወሎና በጎንደር በሚገኙ ታጋይ ወንድሞቻችን ላይ ወንድም በወንድሙ ላይ እንዲነሳና የግድያ ዘመቻ እናካሂድ እንደነበር አልገባንም፤ በጎጃም ቀጠናም ከኮሎኔል ጌታሁን እስከ ማስረሻ ሰጤ ድረስ የምናደርገው የማፈን የመግደል ሙከራ የተሳሳተ መንገድ ነው።

ይሄ ለአፋጎም፣ ለጎጃም ሕዝብም ይሁን ለአማራ ሕዝብ ከባድ ውድቀት እና ድቀት እያስከተለ ነው፤ በትምህርት ጉዳይ ጥያቄ ያነሱ እና ትምህርት ማስጀመር አለብን ካለዛ ከማህበረሰቡ የሚነጥለን አጀንዳ እየመጣ ነው፤ አካሄዳችን መገምገም እና መታረም አለበት ያሉ ግለሰቦች ግፍ እየተፈፀመባቸው ስለመሆኑ ሜዳው ላይ ያሉ ልጆች ሳይቀር ገልፀዋል።

ይሄን ተከትሎም ሐቀኛ ጥያቄ በማቅረባቸው እርምጃ እንዲወሰድባቸው በመተላልፉ የሰላ ትችት ያቀሩቡት አርበኛ ጌራወርቅ ወርቁ በተገኘበት እንዲረሸን የአማራ ፋኖ በጎጃም ወስኗል። አርበኛ ጥላሁን አበጀም እየተሳደደ ነው። የሁለቱንም ዘመቻ ወታደራዊ መምሪያው ኃላፊነቱን ወስዶ እየመራ ነው።

ይሁን እንጅ የ6ኛ ክፍለ ጦር የሕዝብ ግንኙነት የነበረውና መሰል ጥያቄዎችን በማንሳቱ ከክፍለጦሩ ተነስቶ መቆየቱ ይታወቃል። አፋጎ ሰሞኑን ሰሞኑን እንደ አዲስ በገጠመው የውስጣዊ አኔድነት መናጋት መምህር ታደገ ይሁኔን አፍኖታል።

✔️ታደገ ይሁኔ የአፋጎ 6ኛ ህዝብ ግንኙነት በነበረበት ሰዓት በየ አዉደ ዉጊያዎች ያሉ መረጃወችን ሰብሰብ አድርጎ በማህበራዊ ሚዲያ ለትግሉ ደጋፊች ያደርስበት የነበረዉ መንገድ በጣም ሚደነቅበት ነበር።6ኛ ክፍለጦር Reform ሰራ ተብሎ ታደገ ለጊዜዉ ከኃላፊነቱ ተነሳና 5ኛ ክፍለጦር የህዝብ ግንኙነት የነበረ ልጅ አምጥተዉ ሾሙት።

✔️ታደገ ይሁኔን ከሚያቁት ሰዎች ለማጣራት ስሞክር ይኸ ትግል ከሚፈልጓቸዉ ነገሮች ብዙዉን እንደሚያሟላ ትግሉ ከሚንገራገጭበት ምክንያት ዉስጥ እንደሌለበት ተነገረኝ።
✍️ትግሉ እየተንገራገጨ የሚገኘዉ የብልፅግና Double agent የሆኑ ተሰግስገዉበት፣የገንዘብ ሰቀቀናቸዉን የሚሞሉ የተጠራቀሙበት፣አፋጎን የግል ቂም መወጣጫ ያደረጉ ስልቦች የተሰባሰቡበት መሆኑ ነዉ።
✍️መምህር ታደገ ይሁኔ መምህር እንደመሆኑ መጠን ጥሩ ስነ ምግባር እንዳለዉ፣የትግል ጅማሮዉም ከፓርቲ(ባልደራስ ) ያደረገና የፓርቲ ትግል ለዚች ሀገር መፍትሄ እንደማይሆን የተረዳ በሳል ልጅ ነዉ።
✍️ታደገ ይሁኔ የገንዘብ ሰቀቀን የሌለበት ንፁህ ታጋይ ነዉ።ሰዉ ነዉና አያጠፋም አይደለም ያጠፋል ያጠፋ ደግሞ ይጠየቃል።ይኸ ሲባል ግን የመቅጫ ህጉ ሁሉም ጋር እኩል መተግበር ይኖርበታል እንጅ ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የተዘጋጀ መሆን የለበትም።
✍️ታደገ ይሁኔ 6ኛ ላይ የህዝብ ግንኙነት በነበረበት ሰዓት ኃላፊነቱን በአግባቡ ተወጥቷል ወይ ለሚለዉ ለክፍለጦሩ ልተወዉና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚያደረሰን የአዉደ ዉጊያ መረጃዎች ግን ከ9ኙ ክፍለጦሮች በይዘት፣በጥልቀት፣የፁሁፎቹ ፍሰት የተሻለ ነበር። ከባየ ደስታ ጋር በእኩል ደረጃ ሚቀመጥ ልጅ ነዉ በመረጃ አቀራረቡ።

✍️መምህር ታደገን ከኃላፊነት አንስተዉ በሱ ቦታ ሰዉ ሲተኩ መሆን ያለበት Upgrade ነዉ።ሆኖም የመጣዉ ልጅ ከሶስት ቀን በፊት የተደረገን አዉደ ዉጊያ ከሶስት ቀን በኋላ ሰበር ዜና ብሎ የሚያቀርብ አንባቢ እራሱን እንዲጠራጠር የሚያደርግ ዘገምተኛ መደቡ፣ አፋጎ ላይ አንጃ ካልያዝህ ሀቀኛ ታጋይ ከሆንህ በተለይ ለጎጃም ህዝብ ቀጥ ያለ አቋም ካለህ ለላይ አመራሮች ስጋት ነህ።
✍️መምህር ታደገን መጀመሪያ ከኃላፊነት አነሱት ሰዉ ትኩረቱ ትግሉ ላይ ስለነበረ ብዙም ቦታ አልሰጠዉም።ከህዝብ ካራቁት በኋላ እንዲታሰር አደረጉ።ከታሰረ በኋላ የሞትን ፈተና ሁሉ ተጋፈጠ። የጨንጓራ ኬዝ ስለነበረበት በፈጣሪ ታምርና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተደረገ እንቅስቃሴ ለጊዜዉ ተርፏል።

✔️አፋጎ ላይ ያለዉን ችግር ነቅፎ ማዉጣት የነገ ሚባል የቤት ስራ አይደለም።ዝናቡ፣አስረስና አርበኛ ዘመነ ለአፋጎ ድክመትም ጥንካሬም ተጠያቂዎችም ተሞጋሾችም ናቸዉ።

✍️ትናንት አብንን የወቀሱ ብዕሮች ነገ አፋጎን (አርበኛ ዘመነን፣ሻለቃ ዝናቡንና ጠበቃ አስረስን) ሚተዉበት አመክንዮ አይኖራቸዉም።አፋጎ ዉስጥ ያሉ ክፍተቶችን ማስተካከል ያለባቸዉ መሪ ላይ የተቀመጡት ናቸዉ።ከዚያ በተረፈ የሚዲያ ቲፎዞ ለጊዜዉ ካልሆነ የትም አያደርስም።
መምራት ካልተቻለ ደግሞ ለሚመሩ አስረክቦ ኃላፊነትን በፍላጎት መልቀቅ ነዉ።

✔️መምህር ታደገ ይሁኔ ለእስሩ ምክንያት የሆነዉ ከእስክንድር ጋር ታወራለህ ነዉ፣ አጃይብ ነዉ እስክንድር ጎጃም ቀርቶ ሸዋ እነመከታዉ ላይም Irrelevant ከሆነ ቆይቷል።እስክንድር የማሰሪያ ኮድ ሆኖ እንጅ ትክክለኛዉ የእስር ምክንያት የተሻሉ ልጆችን ከትግሉ የማግለል ሴራ ነዉ።በእስክንድር ሰበብ ለአፋጎ ብቻ ሳይሆን ለአማራ ትልቅ አበርክቶ ሚሰጡ ልጆች ተገፍተዋል።

✔️ተጠየቅ ቢኖር ከብልፅግና ጋር አንሶላ ሚጋፈፉ አመራሮች ላይ ነበር።ባል ፋኖ ሚስት ብልፅግና በሆኑበት ድርጅት ተጠያቂነት አለ ለማለት ስለሚከብድ ልጁን ልቀቁትና ወደ ቦታዉ መልሱ።ከዚህ ባለፈ ተድላ ጓሉ፣7ኛ ክፍለጦር፣6ኛ ክፍለጦር ላይ ያላችሁ ራሳችሁን አፅዱ።6ኛ ላይ ያለኸዉ አንተ የፎቶ ሱሰኛ ምተዉህ አይመስለኝም።

N.B አፋጎን በስርዓት እናስተካክለዋለን አልስተካከልም ካለ ደግሞ ራሱን ይበላል አለቀ።ሀቀኛ ታጋይ እየገፉ ብሬንና ስናይቨር ሸጠዉ የበሉትን እሹሩሩ የሚል አንጀኛ ድርጅት አንፈልግም።

ፍቅር አዲስ የሙዚቃዋ ንግስት!!! ሰላም ለኪ ብየ ልጀምርቃሌ እንዲያምርየአገር ተምሳሌት ጎንደር አዛውንቷከእነ ሙሉ ክብሯ ከነምልክቷዘመን ሳይጫነው  ሳያረጅ ወባቷዛሬም እንዳለ ነው ፍቅርና እ...
27/08/2025

ፍቅር አዲስ የሙዚቃዋ ንግስት!!!

ሰላም ለኪ ብየ ልጀምር
ቃሌ እንዲያምር

የአገር ተምሳሌት ጎንደር አዛውንቷ
ከእነ ሙሉ ክብሯ ከነምልክቷ

ዘመን ሳይጫነው ሳያረጅ ወባቷ
ዛሬም እንዳለ ነው ፍቅርና እምነቷ

ኧረ ና ጎንደሬው!

እውቀትም ላዋቂው ሱሪም ለታጣቂው
ክብርና ኩራት ነው ሀገር ለጠባቂው

ጎንደር በደጆቿ፥ በ12ቱ በር
ፍቅር እየገባ፥ ይንጎባለል ነበር

የተነሳው ሲሔድ፤ የሔደው ሲመጣ
በጌምድሬው ያውጣው፤ የጎንደሬን እጣ

እህህ ና ልንገርህ:-

ልጆቿ ዘንግተን ካለሰነፍን በቀር
ከፍ ከፍ ብላ መነሳቷም አይቀር

እናመሰግናለን ፍቅረ አዲስ !!!!
በዚህ ሊንክ እየገባችሁ አድምጡት !

Lyrics Writer- Tesfa BirhanMelody Writer- Abebe BirhaneArrangement- Abegaz ShiwotaMixing- Abegaz ShiwotaMastering- Charlie Pilzer (Tonal Park Studio)Instrume...

Address

Amhara
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bilen mesfin posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category